የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የግብር ክፍያ ሥርዓቱን ከሙስና የፀዳ ለማድረግ የተጀመሩ የዲጂታል አሰራሮች ሊጠናከሩ ይገባል

May 21, 2025

IDOPRESS

ጎንደር/ገንዳ ውሃ፤ግንቦት 12/2017 (ኢዜአ)፦የግብር ክፍያ ሥርዓቱን ከሙስናና ብልሹ አሰራር የጸዳ ለማድረግ የተጀመረው የዲጂታል አሰራር በወረዳ ደረጃም እንዲተገበር በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ጠየቁ።


"ለሁለንተናዊ ብልጽግና የንግዱ ማህበረሰብ ሚና" በሚል መሪ ሀሳብ በጎንደር እና በመተማ ከተሞች ከንግዱ ማህበረሰብ አባላት ጋር የምክክር መድረክ ተካሄዷል።


በጎንደር ከተማ በተካሄደ መድረክ የተሳተፉት አቶ ጎበዜ መሀመድ፤ በክልሉ የተጀመረው ዲጂታል የግብር ክፍያና የንግድ ምዝገባ አገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት ወደ ወረዳዎች በፍጥነት ተደራሽ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል።


ዘመናዊ የአገልግሎት አሰጣጥን መተግበር ለንግዱ ማህበረሰብም ሆነ ለመንግሥት የግብር አሰባሰብ መቀላጠፍ ፋይዳው የጎላ በመሆኑ እስከታችኛው መዋቅር ድረስ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።


የአገልግሎቱ በቴክኖሎጂ መደገፍ የነጋዴውን ተወዳዳሪነት ከማሳደግ ባለፈ የመልካም አስተዳደር ቅሬታን መፍታት እንደሚያስችል የተናገሩት ደግሞ አቶ ለማ ጌታነህ ናቸው።


በተለይ የመሰረተ ልማት አገልግሎቶችን በወረዳዎች በማሟላት የንግዱን ስርዓት ማዘመን ላይ ይበልጥ ሊተኮር ይገባል ብለዋል።


ሌላው ተሳታፊ አቶ ሰዒድ መሀመድ በበኩላቸው፥ ህገ ወጥ ንግድን ለመከላከል የተጀመረው ጥረት መጠናከር እንዳለበት ተናግረዋል።


ቀጣይነት ላለው የኢኮኖሚ እድገት የድርሻቸውን እንደሚወጡ የገለጹት ደግሞ በምዕራብ ጎንደር ዞን መተማ ወረዳ ነዋሪ አቶ አደም ይመር ናቸው።


ለተግባራዊነቱም ህጋዊነትን የተላበሰ የንግድ እንቅስቃሴ እንዲጠናከር የበኩላቸውን እንደሚወጡ አክለዋል።


የመተማ ዮሐንስ ከተማ ነዋሪ አቶ አስማማው ሲሳይ በበኩላቸ፥ የከተሞች እድገትና ውበት ነጋዴውን የሚያነቃቁ ናቸው ብለዋል።


የከተማዋን እድገት ለማስቀጠል ሰላም ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፥ ለሰላምና ጸጥታ መከበር ኃላፊነታቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል።


በተለያዩ ሴክተሮች የተጀመረው ዲጂታል አሰራር በሁሉም መዋቅሮች መስፋፋት እንዳለበት ጠቁመዋል።


በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ይርጋ ሲሳይ፥ የንግዱ ማህበረሰብ የቀልጣፋና ዘመናዊ አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆን የተጀመሩ የተቋማት የሪፎርም ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።


በክልሉ ሰላምን በዘላቂነት በማስፈን ህዝቡን በኢኮኖሚና በማህበራዊ ልማት ዘርፎች ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች እንደሚጠናከሩም ተናግረዋል።


የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አወቀ አስፈሬ እንዳሉት፤ የንግዱን ማህበረሰብ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችና ቅሬታዎች ደረጃ በደረጃ ለመፍታት የሚያስችሉ ስራዎች እየተሰሩ ነው።


ጽንፈኛው ተሽከርካሪዎችን በማቃጠል ኢኮኖሚያዊ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን ጠቁመዋል።


ችግሩን ለመፍታት በሚደረገው ጥረትም የንግዱ ማህበረሰብ የበኩሉን እንዲወጣም አሳስበዋል።


የምዕራብ ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አንዳርጌ ጌጡ እንዳሉት፤ የአካባቢውን ሰላም ለማጠናከር በሚከናወኑ ሥራዎች የንግዱ ማህበረሰብ ከመንግስት ጎን በመሆን የጎላ ሚና ማበርከት ይኖርበታል።


በምክክር መድረኮቹ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችና የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ተሳታፊ ሆነዋል።


#Ethiopian_News_Agency


#ኢዜአ


#Ethiopia

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026