
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 15/2017(ኢዜአ)፦ አይ ዲ ፎር አፍሪካ ጉባኤ የአፍሪካ ሀገራት ኢትዮጵያ በሀገር በቀል ዕውቀት አልምታ ከተገበረችው የዲጂታል መታወቂያ ልምድ ለመቅሰም ጥያቄ ማቅረባቸውን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ዮዳሔ አርአያሥላሴ ገለፁ።
ለአራት ተከታታይ ቀናት በአዲስ አበባ ሲካሄድ የነበረው አይ ዲ ፎር አፍሪካ ዓመታዊ ጉባኤ ተጠናቋል።

በጉባኤው የተለያዩ ሀገራት በዲጂታል ማንነትና መሰረተ ልማት ግንባታ ያላቸውን ተሞኮሮ ያካፈሉባቸው የፖናል ውይይቶችና ባዛሮች መካሄዳቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያም በሀገር በቀል ዕውቀት በታገዘ ቴክኖሎጂ ይፋ ያደረገችው ዲጂታል መታወቂያ የበርካታ አፍሪካ ሀገራትን ቀልብ ስቧል።

የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ዮዳሔ አርአያሥላሴ የጉባኤውን መጠናቀቅ አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ ኢትዮጵያ ሀገር በቀል ዕውቀትን ተጠቅማ ያለማችው የዲጂታል መታወቂያ ቴክኖሎጂ ከበርካታ ሀገራት አድናቆት እንደተቸረው ተናግረዋል።
በዚህም በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ኢትዮጵያ በዲጂታል መታወቂያ ያካበተችውን የቴክኒክና የዕውቀት ድጋፍ መጠየቃቸውንና ኢትዮጵያም ከጉባኤው ተሳታፊ ሀገራት ልምዶች መቅሰሟን ገልጸዋል።
የአይ ዲ ፎር አፍሪካ መስራችና ሊቀመንበር ጆሴፍ አቲክ(ዶ/ር) በበኩላቸው ጉባኤው የአፍሪካን የዲጂታል ሽግግር ስኬትና ቀሪ ስራዎች ላይ ባለድርሻ አካላት በስፋት መምከራቸውን ተናግረዋል።

በአፍሪካ የዲጂታል ማንነት ግንባታ እያደገ መምጣቱን ገልፀው፤ በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ የተሻለ አፈፃፀም ማሳየቷን አንስተዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን ለማሟላት ያከናወናቸው ተግባራት ለዲጂታል ሽግግር የሰጠውን ትኩረት ያመላክታል ሲሉም ገልጸዋል።
አይ ዲ ፎር አፍሪካ ዓመታዊ ጉባኤ ከሁለት ሺህ በላይ የተለያዩ ሀገራት ተሳታፊዎች የታደሙበት ነበር።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026