የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ የባለሀብቱ ጥያቄ እየተመለሰ በመሆኑ አበረታች ውጤት ተመዝግቧል-አቶ ጥላሁን ከበደ

May 26, 2025

IDOPRESS

ሶዶ፤ግንቦት 16/2017 (ኢዜአ)፦በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ባለሀብቶች የሚያነሷቸውን ጥያቄዎች ለመፍታት በተሰራው ስራ አበረታች ውጤቶች መመዝገቡን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ አስታወቁ።


ርዕሰ መስስተዳድሩ በወላይታ ሶዶ ከተማ የሚገኙ ኢንዱስትሪዎችን በተመለከቱበት ወቅት እንዳሉት፥ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ከተጀመረ ወዲህ ባለሀብቶችን በማወያየት ለስራቸው ማነቆ የሆኑ ጉዳዮችን ለመፍታት ሲሰራ ቆይቷል።


በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ያሉ ጸጋዎችን አሟጦ በመጠቀም የምርት መጠንና ጥራትን አሳድጎ ከውጭ የሚገባውን ምርት በሀገር ውስጥ ለመተካት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።


በዘርፉ የተፈጠረውን መነቃቃት ለማስቀጠል ባለሀብቱ የሚያነሳውን ጥያቄ ለመፍታት የክልሉ መንግስት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ተናግረዋል።


ባለፉት 10 ወራት በክልሉ 13 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት ምርት ተመርቶ ለውጭ ገበያ መቅረቡን የተናገሩት ደግሞ የክልሉ ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ቦጋለ ቦሼ (ዶ/ር) ናቸው።


በተያዘው ዓመትም 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ዋጋ ያለው ተኪ ምርት መመረቱንም አስታውቀዋል።


ጉብኝቱ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ባለሀብቶች የሚያነሱትን ችግር በመመልከት የገበያ፣ የአቅርቦት እና የሃይል እንዲሁም ሌሎችን ችግሮች ለመፍታት ያለመ መሆኑንም ገልጸዋል።


በዱቄትና ዳቦ ማምረት ስራ የተሰማራው የኖሚና ትሬዲንግ ባለቤት አቶ አወል ሸረፈዲን፤ በ2008 ዓ.ም በ70 ሚሊዮን ብር ካፒታል የጀመሩት ስራ አሁን ወደ ግማሽ ቢሊዮን ብር ማደጉን ተናግረዋል።


ፋብሪካው ለ270 ሰዎች የስራ ዕድል መፍጠሩንና ዱቄት፣ ዳቦ፣ ኬክና ሌሎች ምርቶችን ለተጠቃሚዎች እያቀረበ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።


በቀጣይ ፖስታ እና ማኮሮኒ ለማምረት የማስፋፊያ ስራ መጀመራቸውን ገልጸው፥ ለስራው ስኬታማነት መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ መሆኑን አስረድተዋል።


በሳሙና ማምረት ስራ ላይ የተሰማሩት አቶ ኤልያስ ኦጃሞ በበኩላቸው፥ ስራውን በ1 ሚሊዮን ብር መጀመራቸውን ገልጸዋል።


በአሁኑ ወቅት ካፒታላችን ከ50 እስከ 60 ሚሊዮን ይደርሳል ያሉት ባለሀብቱ፥ ፋብሪካው ለ60 ሰራተኞች ቋሚና ጊዜያዊ ስራ መፍጠሩን ተናግረዋል።


ለፋብሪካው የጥሬ እቃዎች ማምረቻና ለካርቶን ዝግጅት የሚሆን ተጨማሪ የማስፋፊያ ቦታ ጠይቀው ምላሽ እየተጠባበቁ መሆናቸውንም ገልጸዋል።


የማስፋፊያ ስራው ሲጠናቀቅ ከ200 ለሚልቁ ሰዎች የስራ ዕድል ይፈጠራል ተብሎ እንደሚጠበቅም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026