የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የማሻ ከተማ ነዋሪዎች የሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደገው ነው

May 26, 2025

IDOPRESS

ሚዛን አማን፤ ግንቦት 17/2017 (ኢዜአ)፡-የሌማት ትሩፋት መርሀ ግብር ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደገው መምጣቱን በሸካ ዞን በዘርፉ የተሰማሩ የማሻ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።

በዶሮ እርባታ የተሰማራው ወጣት አማኑኤል ኃይሌ ባለፉት ሦስት ዓመታት ለሥጋና ለእንቁላል የሚሆኑ ዶሮዎችን ለገበያ እያቀረበ መሆኑን ተናግሯል።

ሥራውን ከጀመረ ወዲህ ከ14 ሺህ በላይ ታዳጊ ዶሮዎችን እንዳሰራጨና በአሁን ወቅትም 2ሺህ ዶሮዎች ለሽያጭ ማዘጋጀቱን ጠቅሷል።

በአካባቢው ገበያ ያለውን የእንቁላል ፍላጎት በመረዳት 1ሺህ የእንቁላል ጣይ ዶሮዎችን በማርባት ወደሥራው መግባታቸውን የተናገሩት ደግሞ ሌላው የከተማዋ ነዋሪ አቶ ብርሃኑ ሀይሌ ናቸው።


በማር ምርት ሥራ ላይ ከተሰማሩት መካከል ከ50 በላይ ዘመናዊ ቀፎዎችን በማዘጋጀት ንብ የማነብ ሥራ መጀመሩን የገለጸው ደግሞ ወጣት ታጠቅ ሠራዊት ነው።

ከአንድ ዘመናዊ የንብ ቀፎ 30 ኪሎ ግራም ማር በማግኘት ገቢውን ለማሳደግ ጠንክሮ እየሰራ መሆኑንም ጠቁሟል።


የማሻ ከተማ አስተዳደር ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አስማማው ታምሩ "በቤተሰብ ደረጃ የተሟላ ማዕድ እንዲኖር የሚያስችለውን የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭ ስኬታማ ለማድረግ በትኩረት እየተሠራ ነው" ብለዋል።


በከተማው ኢኒሼቲቩን አስፋፍቶ ለማስቀጠል የሌማት ትሩፋት መንደር የማደራጀት ተግባር እየተከናወነ መሆኑን አመልክተዋል።

የሸካ ዞን ግብርና፣ ደን፣ አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ መምሪያ ኃላፊ አቶ አዕምሮ ደሳለኝ በበኩላቸው እንዳሉት በዋና ዋና የሌማት ትሩፋት ዘርፎች ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሠራ ነው።


ለእዚህም በዞኑ በሦስት ወረዳዎችና ሁለት የከተማ አስተዳደሮች ከ120 በላይ የሌማት ትሩፋት መንደሮች መደራጀታቸውን በማሳያነት ጠቅሰዋል።

እነዚህን መንደሮች ሞዴል ለማድረግ እንደሚሰራ ጠቁመው ለዚህም በዞኑ በኩል የሙያና የቁሳቁስ ድጋፍ እንደሚደረግ አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026