
አዲስ አበባ፤ግንቦት 19/2017 (ኢዜአ)፦በ2017 ብሔራዊ የሳይበር ስልጠና መሳተፍ የሚፈልጉ ባለተሰጥኦዎች እስከ ግንቦት 24 እንዲመዘገቡ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጥሪ አቀረበ።
አስተዳደሩ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጠው መግለጫ ብሔራዊ የሳይበር ተሰጥኦ ውድድር ከሐምሌ አንድ ጀምሮ እንደሚካሄድ አስታውቋል።
በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የሳይበር ልህቀት ማዕከል ዳይሬክተር ቢሻው በየነ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥አስተዳደሩ ባለፉት ሶስት ዓመታት ለታዳጊ ወጣቶች ተከታታይ ስልጠናዎችን እየሰጠ ነው።
የ2017 ብሔራዊ የሳይበር ተሰጥኦ ውድድር በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ4ኛ ጊዜ እንደሚካሄድ ተናግረዋል።
በሁሉም የሀገሪቱ ክፍል የሚገኙና እድሜያቸው ከ11 ዓመት ጀምሮ በስልጠናው መሳተፍ እንደሚችሉ ገልጸው፥ እስከ ግንቦት 24/2017 ዓ.ም እንዲመዘገቡም ጥሪ አቅርበዋል።
መላው ኢትዮጵያውያን ወጣቶች በዚህ ስልጠና በንቃት እንዲሳተፉ የጠየቁት ዳይሬክተሩ፥ ተመዝጋቢዎች በ https://talent.insa.gov.et በመግባት መመዝገብ እንደሚችሉ ጠቁመዋል።
በ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና የወሰዱ ዜጎች የተሻለ እድል እንዳላቸውም ገልጸዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026