
አዲስ አበባ፤ግንቦት 19/2017 (ኢዜአ)፦በ2017 ብሔራዊ የሳይበር ስልጠና መሳተፍ የሚፈልጉ ባለተሰጥኦዎች እስከ ግንቦት 24 እንዲመዘገቡ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጥሪ አቀረበ።
አስተዳደሩ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጠው መግለጫ ብሔራዊ የሳይበር ተሰጥኦ ውድድር ከሐምሌ አንድ ጀምሮ እንደሚካሄድ አስታውቋል።
በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የሳይበር ልህቀት ማዕከል ዳይሬክተር ቢሻው በየነ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥አስተዳደሩ ባለፉት ሶስት ዓመታት ለታዳጊ ወጣቶች ተከታታይ ስልጠናዎችን እየሰጠ ነው።
የ2017 ብሔራዊ የሳይበር ተሰጥኦ ውድድር በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ4ኛ ጊዜ እንደሚካሄድ ተናግረዋል።
በሁሉም የሀገሪቱ ክፍል የሚገኙና እድሜያቸው ከ11 ዓመት ጀምሮ በስልጠናው መሳተፍ እንደሚችሉ ገልጸው፥ እስከ ግንቦት 24/2017 ዓ.ም እንዲመዘገቡም ጥሪ አቅርበዋል።
መላው ኢትዮጵያውያን ወጣቶች በዚህ ስልጠና በንቃት እንዲሳተፉ የጠየቁት ዳይሬክተሩ፥ ተመዝጋቢዎች በ https://talent.insa.gov.et በመግባት መመዝገብ እንደሚችሉ ጠቁመዋል።
በ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና የወሰዱ ዜጎች የተሻለ እድል እንዳላቸውም ገልጸዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026