
አዲስ አበባ፤ግንቦት 19/2017 (ኢዜአ)፦በ2017 ብሔራዊ የሳይበር ስልጠና መሳተፍ የሚፈልጉ ባለተሰጥኦዎች እስከ ግንቦት 24 እንዲመዘገቡ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጥሪ አቀረበ።
አስተዳደሩ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጠው መግለጫ ብሔራዊ የሳይበር ተሰጥኦ ውድድር ከሐምሌ አንድ ጀምሮ እንደሚካሄድ አስታውቋል።
በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የሳይበር ልህቀት ማዕከል ዳይሬክተር ቢሻው በየነ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥አስተዳደሩ ባለፉት ሶስት ዓመታት ለታዳጊ ወጣቶች ተከታታይ ስልጠናዎችን እየሰጠ ነው።
የ2017 ብሔራዊ የሳይበር ተሰጥኦ ውድድር በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ4ኛ ጊዜ እንደሚካሄድ ተናግረዋል።
በሁሉም የሀገሪቱ ክፍል የሚገኙና እድሜያቸው ከ11 ዓመት ጀምሮ በስልጠናው መሳተፍ እንደሚችሉ ገልጸው፥ እስከ ግንቦት 24/2017 ዓ.ም እንዲመዘገቡም ጥሪ አቅርበዋል።
መላው ኢትዮጵያውያን ወጣቶች በዚህ ስልጠና በንቃት እንዲሳተፉ የጠየቁት ዳይሬክተሩ፥ ተመዝጋቢዎች በ https://talent.insa.gov.et በመግባት መመዝገብ እንደሚችሉ ጠቁመዋል።
በ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና የወሰዱ ዜጎች የተሻለ እድል እንዳላቸውም ገልጸዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026