የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ዩኒቨርሲቲው በጥናትና ምርምር ላይ በማተኮር ለትምህርት ጥራቱ መሻሻል አስተዋጽኦ እያረከተ ነው

Jun 3, 2025

IDOPRESS

ደሴ፤ ግንቦት 22/2017(ኢዜአ)፡- ወሎ ዩኒቨርሲቲ በቴክኖሎጂ የታገዘ ተግባር ተኮር ትምህርት ከመስጠት ባሻገር ለትምህርት ጥራቱ መሻሻል ጥናትና ምርምር ላይ በማተኮር አስተዋጽኦ እያረከተ መሆኑን አስታወቀ።

ዩኒቨርሲቲው 5ኛውን "የመምህራን፣ ትምህርትና ስነ ባህሪ" ሀገር አቀፍ ጥናትና ምርምር ጉባኤ በደሴ ከተማ እያካሄደ ነው፡፡


በጉባኤው የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ብርሃን አስማሜ(ዶ/ር) እንደገለጹት ተቋሙ በቴክኖሎጂ የታገዘ ተግባር ተኮር ትምህርት በመስጠት ላይ አተኩሮ እየሰራ ነው።

ለመማር ማስተማር ስራው የሚያግዙ የተለያዩ ጥናትና ምርምሮችን በማካሄድ የትምህርት ጥራትንን ለማረጋገጥ የበኩሉን እየተወጣ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

መምህራን ከተማሪዎች ጋር ያላቸውን ተግባቦት በማሳደግ፣ ክህሎትና እውቀታቸውን በማዳበር የተሳለጠ መማር ማስተማሩን ለማሳለጥ እየሰራ መሆኑን አስረድተዋል።


በዩኒቨርሲቲው የመምህራን ትምህርትና ስነ-ባህሪ ተቋም ዲን ጌታቸው ጣሰው(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ዩኒቨርሲቲው በቴክኖሎጂ፣ በጥናትና ምርምር በመታገዝ ብቁ ዜጋ ለማፍራት እየሰራ ይገኛል።

በጉባኤው በመማር ማስተማሩ ዘርፍ ስምንት ጥናታዊ ጽህፎች ቀርበው ውይይት እንደሚደረግባቸው ጠቁመው፤ የጥናቶቹን ግኝቶች መሰረት በማድረግ ወደ ተግባር እንዲቀየሩ በትኩረት ይሰራል ብለዋል፡፡


የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የገጠር ትምህርት ቤቶችን ያማከለ የትምህርት ስርዓት መዘርጋት ይገባል ያሉት ደግሞ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሳይኮሎጅ መምህርና ተመራማሪ ፕሮፌሰር በላይ ተፈራ ናቸው፡፡

ዘመናዊውን የመማር ማስተማር ዘዴን ከሀገር በቀል እውቀት ጋር ጭምር በማጣጣም ባህሉንና እሴቱን የጠበቀ፣ በስነ ምግባር የታነጸ፣ በክህሎት የዳበር ትውልድ ማፍራት ይገባል ብለዋል፡፡


በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ኮምሽን የምርምር ሥራ አስፈጻሚ ፕሮፌሰር ያለው እንዳወቅ፤ በቴክኖሎጂ የታገዘ ተግባር ተኮር ትምህርትን በማስፈን የኢትዮጵያን እድገት ማፋጠን እንደሚገባ አመልክተዋል።

ይህምትውልዱ ጠቃሚ ሀሳብ ማፍለቅንና አብሮነትን የሚያጎለብት እንዲሆን ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በምርምር መደገፍም ተገቢ መሆኑን ተናግረዋል።

ከዛሬ ጀምሮ ለሁለት ቀናት በሚካሄደው ጉባኤ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ምሁራንና ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ሲሆን፤ ጥናታዊ ጽሑፎች እንደሚቀርቡም ይጠበቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026