
ጅማ፣ግንቦት 24/2017(ኢዜአ)፦በጅማ ከተማ 47 የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት ዝግጁ መሆናቸውን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።
የጅማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጣሃ ቀመር እንዳሉት፥ አስተዳደሩ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ በጥራት ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ እየተደረገ ነው፡፡
ፕሮጀክቶቹ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ ባሻገር የከተማዋን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚያግዙ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
የግንባታ ስራቸው ከተጠናቀቁ ፕሮጀክቶች መካከል ሼዶች፣ የኢንዱስትሪ ማእከሎች፣ የውስጥ ለውስጥ መንገድና የኮሪደር ልማት ስራዎች ይገኙበታል፡፡
በመንግስት በጀትና በህብረተሰቡ ተሳትፎ የተገነቡ እነዚሁ የልማት ፕሮጀክቶች በግንባታ ሂደታቸውም ከ12 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች የስራ እድል መፍጠራቸውን አመልክተዋል፡፡
አስተያየታቸውን ከሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ኪሩቤል ታረቀኝ በሰጠው አስተያየት በከተማዋ በኮሪደርና በሌሎች የልማት ስራዎች የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ የስራ እድል መፈጠሩን ተናግሯል፡፡
በከተማ አስተዳደሩ ተገንብተው ለአገልግሎት የበቁት የመሰረተ ልማት ስራዎች ከተማዋን ውብና ሳቢ እንድትሆን ከማድረግ ባለፈ የስራ ዕድል መፍጠራቸውን የገለጹት ደግሞ ሌላው የከተማዋ ነዋሪ አቶ ጋሊ አባ ወሊ ናቸው።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026