
ሚዛን አማን፤ግንቦት 24/2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ለ180 ሺህ አርሶ አደሮች በዘመናዊ የመሬት ልኬትና ሰርቲፍኬሽን ሥርዓት የተመዘገበ የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
በክልሉ ቤንች ሸኮ ዞን በሁለተኛ ደረጃ የመሬት ልኬትና ሰርቲፍኬሽን ሥራ መሬታቸውን ላስመዘገቡ አርሶ አደሮች የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር የመስጠት መርሐ ግብር በደቡብ ቤንች ወረዳ ተካሄዷል።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው በወረዳው ቂጤ ቀበሌ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት በክልሉ የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ዘርፍን ለማዘመን በርካታ ተግባራት ሲከናወኑ ቆይቷል።
በዚህም የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት መሠረት በማድረግ ረቂቅ ደንብ መዘጋጀቱን ጠቅሰው "በቅርቡ ጸድቆ ወደ ተግባር ይገባል" ብለዋል።
በክልሉ ባሉ 17 ወረዳዎች በተካሄደው ሁለተኛ ደረጃ የመሬት ልኬትና የይዞታ ማረጋገጫ ሰርቲፍኬሽን ሥራ ከ250 ሺህ በላይ መሬት መለካት መቻሉን ገልጸዋል።
በዚህም በዘመናዊ መንገድ ተለክቶ በዲጂታል ሥርዓት የተመዘገበውን የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ለ180 ሺህ አርሶ አደሮች መሰጠቱን ጠቅሰዋል።
አርሶ አደሮች ባስመዘገቡት ይዞታ ተፈጥሮን እየጠበቁ አልምተው ዓለም አቀፍ ገበያን መቀላቀል የሚያስችል ምርት በማምረት ተጠቃሚነታቸውን እንዲያረጋግጡም አሳስበዋል።
የቤንች ሸኮ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን መሬት የኢኮኖሚ ሁሉ መሠረት በመሆኑ በአግባቡ አስተዳድሮ መጠቀም ይገባል ብለዋል።
አሁን እየተሠራ ያለው ዘመናዊ የመሬት ልኬት ሥርዓት የመሬት ባለቤትነት ዋስትና ከማረጋገጥ ባሻገር የሴቶችን የባለቤትነትና የብድር አገልግሎት መጠቀም መብትን ያረጋገጠ ነው ብለዋል።
በዞኑ ደቡብ ቤንች ወረዳ ቂጤ ቀበሌ በመጀመሪያ ዙር ከተለካ መሬት ውስጥ ከ3 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች በዘመናዊ መንገድ ተመዝግቦ መሰጠቱን ተናግረዋል።
የይዞታ ማረጋገጫ ሰርቲፍኬት ከተረከቡ የቀበሌው አርሶ አደሮች መካከል ወይዘሮ ወርቄ ይሽጉ፥አዲሱ የምዝገባ ስርዓት ተጠቃሚነታችንን የሚያረጋግጥ በመሆኑ ደስተኛ ነኝ ብለዋል።
ከዚህ ቀደም ስራ ላይ ሳይውል የቆየውን መሬትን አስይዞ የመበደር፣ በአግባቡ አልምቶ የመጠቀምና የመሳሰሉ መብቶችን እና ግዴታዎችን ያካተተ ሰርቲፍኬት መረከባቸውን ተናግረዋል።
የምዝገባ ስርዓቱ የወሰን ውዝግብና መሰል የባለቤትነት አለመግባባቶችን የሚቀርፍ ነው ያሉት ደግሞ አቶ ታደለ ሞሊሶ የተባሉ የቀበሌው አርሶ አደር ናቸው።
ከምንም በላይ በቴክኖሎጂ ተደግፎ በዘመናዊ መንገድ ተመዝግቦ ይዞታቸው መረጋገጡ ትልቅ ትርጉም እንዳለው ገልጸው፥ ከማስመዝገብ ባሻገር በአግባቡ አልምተው ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ እንደሚጥሩም አረጋግጠዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026