የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በክልሉ ለ180 ሺህ አርሶ አደሮች የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጥቷል - ቢሮው

Jun 3, 2025

IDOPRESS

ሚዛን አማን፤ግንቦት 24/2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ለ180 ሺህ አርሶ አደሮች በዘመናዊ የመሬት ልኬትና ሰርቲፍኬሽን ሥርዓት የተመዘገበ የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።


በክልሉ ቤንች ሸኮ ዞን በሁለተኛ ደረጃ የመሬት ልኬትና ሰርቲፍኬሽን ሥራ መሬታቸውን ላስመዘገቡ አርሶ አደሮች የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር የመስጠት መርሐ ግብር በደቡብ ቤንች ወረዳ ተካሄዷል።


የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው በወረዳው ቂጤ ቀበሌ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት በክልሉ የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ዘርፍን ለማዘመን በርካታ ተግባራት ሲከናወኑ ቆይቷል።


በዚህም የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት መሠረት በማድረግ ረቂቅ ደንብ መዘጋጀቱን ጠቅሰው "በቅርቡ ጸድቆ ወደ ተግባር ይገባል" ብለዋል።


በክልሉ ባሉ 17 ወረዳዎች በተካሄደው ሁለተኛ ደረጃ የመሬት ልኬትና የይዞታ ማረጋገጫ ሰርቲፍኬሽን ሥራ ከ250 ሺህ በላይ መሬት መለካት መቻሉን ገልጸዋል።


በዚህም በዘመናዊ መንገድ ተለክቶ በዲጂታል ሥርዓት የተመዘገበውን የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ለ180 ሺህ አርሶ አደሮች መሰጠቱን ጠቅሰዋል።


አርሶ አደሮች ባስመዘገቡት ይዞታ ተፈጥሮን እየጠበቁ አልምተው ዓለም አቀፍ ገበያን መቀላቀል የሚያስችል ምርት በማምረት ተጠቃሚነታቸውን እንዲያረጋግጡም አሳስበዋል።


የቤንች ሸኮ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን መሬት የኢኮኖሚ ሁሉ መሠረት በመሆኑ በአግባቡ አስተዳድሮ መጠቀም ይገባል ብለዋል።


አሁን እየተሠራ ያለው ዘመናዊ የመሬት ልኬት ሥርዓት የመሬት ባለቤትነት ዋስትና ከማረጋገጥ ባሻገር የሴቶችን የባለቤትነትና የብድር አገልግሎት መጠቀም መብትን ያረጋገጠ ነው ብለዋል።


በዞኑ ደቡብ ቤንች ወረዳ ቂጤ ቀበሌ በመጀመሪያ ዙር ከተለካ መሬት ውስጥ ከ3 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች በዘመናዊ መንገድ ተመዝግቦ መሰጠቱን ተናግረዋል።


የይዞታ ማረጋገጫ ሰርቲፍኬት ከተረከቡ የቀበሌው አርሶ አደሮች መካከል ወይዘሮ ወርቄ ይሽጉ፥አዲሱ የምዝገባ ስርዓት ተጠቃሚነታችንን የሚያረጋግጥ በመሆኑ ደስተኛ ነኝ ብለዋል።


ከዚህ ቀደም ስራ ላይ ሳይውል የቆየውን መሬትን አስይዞ የመበደር፣ በአግባቡ አልምቶ የመጠቀምና የመሳሰሉ መብቶችን እና ግዴታዎችን ያካተተ ሰርቲፍኬት መረከባቸውን ተናግረዋል።


የምዝገባ ስርዓቱ የወሰን ውዝግብና መሰል የባለቤትነት አለመግባባቶችን የሚቀርፍ ነው ያሉት ደግሞ አቶ ታደለ ሞሊሶ የተባሉ የቀበሌው አርሶ አደር ናቸው።


ከምንም በላይ በቴክኖሎጂ ተደግፎ በዘመናዊ መንገድ ተመዝግቦ ይዞታቸው መረጋገጡ ትልቅ ትርጉም እንዳለው ገልጸው፥ ከማስመዝገብ ባሻገር በአግባቡ አልምተው ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ እንደሚጥሩም አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026