የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የመንግስትና የህዝብ ውስን ሀብት ለታለመለት ዓላማ እንዲውል የምክር ቤት አባላት የክትትልና የቁጥጥር ሥራቸውን ማጠናከር አለባቸው

Jun 5, 2025

IDOPRESS

አርባ ምንጭ፤ ግንቦት 27/2017(ኢዜአ)፦ የመንግስትና የህዝብ ውስን ሀብት ለታለመለት ዓላማ እንዲውል የምክር ቤት አባላት የሚያከናውኑትን የቁጥጥርና የክትትል ሥራ ማጠናከር እንዳለባቸው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ሎሚ በዶ ገለጹ።

ምክትል አፈ-ጉባኤዋ ይህን ያሉት በአርባ ምንጭ ከተማ እየተካሄደ ባለው 23ኛው የፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የዋና ኦዲተሮች እና ባለድርሻ አካላት ዓመታዊ ጉባኤ ላይ ተገኝተው ነው።

በየደረጃው ባሉ የመንግስት ተቋማት ብልሹ አሠራር፣ ህገ-ወጥ ተግባር እና ስልጣንና ሃላፊነትን ያለአግባብ የመጠቀም ዝንባሌ እንደሚስተዋል ጠቅሰው፣ ይህም በሀገራዊ አድገት ላይ ጫና እያሳደረ ይገኛል ብለዋል።


በየደረጃው ያሉ የምክር ቤት አባላትና አፈ ጉባኤዎች በጀት ከማጽደቅ ባለፈ የህዝብና የመንግስት ውስን ሀብት ለታለመለት ዓላማ እንዲውል የሚያከናውኑትን የክትትልና የቁጥጥር ሥራ ማጠናከር እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል።

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ቋሚ ኮሚቴ ከፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ጋር በቅርበት በመስራት የኦዲት ግኝቶችን ከመፈተሽ ባለፈ በአጥፊዎች ላይ ህጋዊና አስተማሪ እርምጃ እንዲወሰድ እየሠራ መሆኑንም ተናግረዋል።

የመንግስት ተቋማትና ሌሎች ድርጅቶችን ከብልሹ አሠራር ለማጽዳት የኦዲት ተቋማት ሚና ጉልህ መሆኑን ጠቅሰው፣ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤቱ ከተቋማዊ ሥራ ባሻገር ለሀገራዊ የኦዲት አሠራር ውጤታማነት ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል።

ህገወጥነትና ብልሹ አሠራሮችን ከማጋለጥ ባለፈ በአጥፊዎች ላይ እርምጃ በመውሰድ የተጀመረው ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ምክትል አፈ ጉባኤዋ ጠቁመዋል።


የፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ በበኩላቸው በየደረጃው ከሚገኙ የህዝብ ተወካዮች ጋር በመቀናጀት የሀገርና የህዝብ ውስን ሀብትን ከምዝበራ ለመታደግ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

ተቋማቸው በክልሎችና በከተሞች አስተዳደር ካሉ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤቶች ጋር ጠንካራ ተዋረዳዊ የሥራ ግንኙነት እንዳለውም ጠቅሰዋል።

የሀገሪቱን የኦዲት ሥራ ይበልጥ ከፍ ለማድረግ ለኦዲተሮች በዓለም አቀፍ ስታንዳርድ መሠረት አቅም የመገንባት ስራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።

በመንግስት ከሚሰሩ ሥራዎች በተጨማሪ ህዝብም ክፍተቶችን ሲያይ ፈጥኖ ጥቆማ በመስጠት የበኩሉን እንዲወጣ ጠይቀዋል።

ለሦስት ቀናት በተዘጋጀው መድረክ የፌደራል፣ የክልል እና የከተሞች ምክር ቤት አፈ ጉባኤዎች፣ የቋሚ ኮሚቴዎች አባላትና ዋና ኦዲተሮች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026