የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የመንግስትና የህዝብ ውስን ሀብት ለታለመለት ዓላማ እንዲውል የምክር ቤት አባላት የክትትልና የቁጥጥር ሥራቸውን ማጠናከር አለባቸው

Jun 5, 2025

IDOPRESS

አርባ ምንጭ፤ ግንቦት 27/2017(ኢዜአ)፦ የመንግስትና የህዝብ ውስን ሀብት ለታለመለት ዓላማ እንዲውል የምክር ቤት አባላት የሚያከናውኑትን የቁጥጥርና የክትትል ሥራ ማጠናከር እንዳለባቸው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ሎሚ በዶ ገለጹ።

ምክትል አፈ-ጉባኤዋ ይህን ያሉት በአርባ ምንጭ ከተማ እየተካሄደ ባለው 23ኛው የፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የዋና ኦዲተሮች እና ባለድርሻ አካላት ዓመታዊ ጉባኤ ላይ ተገኝተው ነው።

በየደረጃው ባሉ የመንግስት ተቋማት ብልሹ አሠራር፣ ህገ-ወጥ ተግባር እና ስልጣንና ሃላፊነትን ያለአግባብ የመጠቀም ዝንባሌ እንደሚስተዋል ጠቅሰው፣ ይህም በሀገራዊ አድገት ላይ ጫና እያሳደረ ይገኛል ብለዋል።


በየደረጃው ያሉ የምክር ቤት አባላትና አፈ ጉባኤዎች በጀት ከማጽደቅ ባለፈ የህዝብና የመንግስት ውስን ሀብት ለታለመለት ዓላማ እንዲውል የሚያከናውኑትን የክትትልና የቁጥጥር ሥራ ማጠናከር እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል።

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ቋሚ ኮሚቴ ከፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ጋር በቅርበት በመስራት የኦዲት ግኝቶችን ከመፈተሽ ባለፈ በአጥፊዎች ላይ ህጋዊና አስተማሪ እርምጃ እንዲወሰድ እየሠራ መሆኑንም ተናግረዋል።

የመንግስት ተቋማትና ሌሎች ድርጅቶችን ከብልሹ አሠራር ለማጽዳት የኦዲት ተቋማት ሚና ጉልህ መሆኑን ጠቅሰው፣ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤቱ ከተቋማዊ ሥራ ባሻገር ለሀገራዊ የኦዲት አሠራር ውጤታማነት ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል።

ህገወጥነትና ብልሹ አሠራሮችን ከማጋለጥ ባለፈ በአጥፊዎች ላይ እርምጃ በመውሰድ የተጀመረው ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ምክትል አፈ ጉባኤዋ ጠቁመዋል።


የፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ በበኩላቸው በየደረጃው ከሚገኙ የህዝብ ተወካዮች ጋር በመቀናጀት የሀገርና የህዝብ ውስን ሀብትን ከምዝበራ ለመታደግ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

ተቋማቸው በክልሎችና በከተሞች አስተዳደር ካሉ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤቶች ጋር ጠንካራ ተዋረዳዊ የሥራ ግንኙነት እንዳለውም ጠቅሰዋል።

የሀገሪቱን የኦዲት ሥራ ይበልጥ ከፍ ለማድረግ ለኦዲተሮች በዓለም አቀፍ ስታንዳርድ መሠረት አቅም የመገንባት ስራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።

በመንግስት ከሚሰሩ ሥራዎች በተጨማሪ ህዝብም ክፍተቶችን ሲያይ ፈጥኖ ጥቆማ በመስጠት የበኩሉን እንዲወጣ ጠይቀዋል።

ለሦስት ቀናት በተዘጋጀው መድረክ የፌደራል፣ የክልል እና የከተሞች ምክር ቤት አፈ ጉባኤዎች፣ የቋሚ ኮሚቴዎች አባላትና ዋና ኦዲተሮች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026