የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የአሰላ ከተማን እድገትና የነዋሪዎቿን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎች እየተፋጠኑ ነው

Jun 6, 2025

IDOPRESS

አዳማ፤ ግንቦት 28/2017(ኢዜአ)፦ የአሰላ ከተማን እድገትና የነዋሪዎቿን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎች እየተፋጠኑ መሆኑን የከተማው አስተዳደር አስታወቀ።

የአሰላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ስሜ ፀጋዬ ለኢዜአ እንደገለፁት የከተማዋን ነዋሪ የልማት ጥያቄ ለመመለስ በትኩረት እየተሰራ ነው።

በዚህም በከተማዋ የኮሪደር ልማት፣ መናኸሪያ፣ ትምህርት ቤቶች፣ የጤና ተቋማትና የመዝናኛ ማዕከላት ግንባታ እንዲሁም የወንዝ ዳርቻዎችን ፅዱ የማድረግ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

የከተማዋን እድገት በማቀላጠፍ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ለማድረግ ያለመ የመጀመሪያው ዙር 25 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት መገንባቱንም አስረድተዋል።

ከሁለተኛው ዙር የ16 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ ውስጥም የ2 ኪሎ ሜትር የአስፋልት ኮንክሪት ግንባታ በቀጣዩ ወር እንደሚጠናቀቅ ጠቁመዋል።

የአሰላ ከተማን ከሚያቋርጡ አምስቱ ወንዞች በሁለቱ ላይ የወንዝ ዳርቻ ልማት እየተሰራ ነው ብለዋል።

በተጨማሪም በከተማ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚያስችሉ የዶሮና ወተት ላሞች እርባታ ማዕከላት ተገንብተው መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል።

በከተማዋ ለተመዘገበው የልማት ውጤት ባለሃብቶችን ጨምሮ ህብረተሰቡ በሁሉም መስክ እያደረጉ ላለው ተሳትፎ ከንቲባው አመስግነዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025