የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የአሰላ ከተማን እድገትና የነዋሪዎቿን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎች እየተፋጠኑ ነው

Jun 6, 2025

IDOPRESS

አዳማ፤ ግንቦት 28/2017(ኢዜአ)፦ የአሰላ ከተማን እድገትና የነዋሪዎቿን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎች እየተፋጠኑ መሆኑን የከተማው አስተዳደር አስታወቀ።

የአሰላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ስሜ ፀጋዬ ለኢዜአ እንደገለፁት የከተማዋን ነዋሪ የልማት ጥያቄ ለመመለስ በትኩረት እየተሰራ ነው።

በዚህም በከተማዋ የኮሪደር ልማት፣ መናኸሪያ፣ ትምህርት ቤቶች፣ የጤና ተቋማትና የመዝናኛ ማዕከላት ግንባታ እንዲሁም የወንዝ ዳርቻዎችን ፅዱ የማድረግ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

የከተማዋን እድገት በማቀላጠፍ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ለማድረግ ያለመ የመጀመሪያው ዙር 25 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት መገንባቱንም አስረድተዋል።

ከሁለተኛው ዙር የ16 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ ውስጥም የ2 ኪሎ ሜትር የአስፋልት ኮንክሪት ግንባታ በቀጣዩ ወር እንደሚጠናቀቅ ጠቁመዋል።

የአሰላ ከተማን ከሚያቋርጡ አምስቱ ወንዞች በሁለቱ ላይ የወንዝ ዳርቻ ልማት እየተሰራ ነው ብለዋል።

በተጨማሪም በከተማ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚያስችሉ የዶሮና ወተት ላሞች እርባታ ማዕከላት ተገንብተው መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል።

በከተማዋ ለተመዘገበው የልማት ውጤት ባለሃብቶችን ጨምሮ ህብረተሰቡ በሁሉም መስክ እያደረጉ ላለው ተሳትፎ ከንቲባው አመስግነዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026