የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በኢትዮጵያ የኒውክሌር ቴክኖሎጂን ለጤና፣ለግብርናና ለኃይል አቅርቦት ዘርፎች መጠቀም የሚያስችል ጥናትና ምርምር እየተደረገ ነው

Jun 9, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ግንቦት 30/2017(ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የአፍሪካ ኒውክሌር ሳይንስና ቴክኖሎጂ ማዕከል ሆኖ መመረጡ ይታወቃል።


በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የኒውክሌር ቴክኖሎጂ ማዕከል ኃላፊ ደረጃው አየለ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፥ዩኒቨርሲቲው ከኒውክሌር ኢነርጂ ሰላማዊ የኃይል አማራጭ ተጠቃሚ የሚያደርጋትን የልህቀት ማዕከላት ገንብቷል፡፡


ዩኒቨርሲቲው የአፍሪካ የኒውክሌር ሳይንስ ማዕከል ሆኖ መመረጡ በዘርፉ ስኬታማ የጥናትና ምርምር ስራዎችን ለመሥራት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል።


በማዕከሉ በተለያዩ የምርምር መስኮች ላይ ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በመተባበር ትልልቅ የጥናትና ምርምር ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን አስታውቀዋል።


በቀጣይም በኒውክሌር ቴክኖሎጂ ዕውቀትና ክህሎትን ካካበቱ የሩሲያ፣ ኮሪያና ቻይና ተመራማሪና የልህቀት ማዕከላት ጋር ጠንካራ ትብብር በመፍጠር እንደሚሰራ ገልጸዋል።


በኢትዮጵያ የኒውክሌር ቴክኖሎጂን ለጤና፣ለግብርናና ለኃይል አቅርቦት ዘርፎች መጠቀም የሚያስችል ጥናትና ምርምር እየተካሄደ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡


በዩኒቨርስቲው የ2ተኛ ዓመት የኒውክሌር ሳይንስ ኢንጂነርንግ ተማሪ ቴዎድሮስ አበባው፥ በዩኒቨርሲቲው የኒውክሌር ትምህርት መሰጠቱ ኢትዮጵያን በዘርፉ ተጠቃሚ የሚያደርግ ዕውቀትና ክህሎት ያለው ዜጋ ለማፍራት ትልቅ ዕድል መፍጠሩን ገልጿል።


የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የአፍሪካ የኒውክሌር ሳይንስና ቴክኖሎጂ ማዕከል ሆኖ የተመረጠ ሲሆን በመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎችን ተቀብሎ በማስተማር ላይ ይገኛል።


በሚያዝያ ወር መጨረሻ የዓለም አቀፍ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲና የቻይናው ሽንግዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር፣በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ሥር የአፍሪካ ኒውክሌር ሳይንስ ማዕከል እንዲቋቋም ስምምነት ማድረጋቸው ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026