አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2017(ኢዜአ)፦ የአንበሳ ጋራዥ-ጃክሮስ-ጎሮ አደባባይ የኮሪደር ሥራ ከፍተኛ የፍሰት ጭንቅንቅ የነበረበትን ከባቢ ቀይሮታል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት የእግረኛ መንገዶች፣ የብስክሌት መንገዶች፣ የመኪና ማቆሚያዎች፣ የሕፃናት መጫወቻዎች፣ ሱቆች፣ የሕዝብ ማረፊያ ፕላዛዎች፣ የሕዝብ መጸዳጃዎች፣ የተለዩ የታክሲ እና የአውቶቡስ ቤዮች መሠራት አካባቢውን የበለጠ ተደራሽ፣ አካታች እና ለመኖር ምቹ አድርጎ እንደገና የገነባ ተግባር ነው ብለዋል።
የከተማም ሆነ የገጠር ኮሪደር ሥራዎች የከበረ የሰውልጅ የአኗኗር ዘይቤን ያስተዋወቀ እና ፍትኃዊ የሕዝባዊ ስፍራዎች አጠቃቀምን በመፍጠርም ማኅበረሰቦችን ከፍ ያደረገ ነው ሲሉ ገልጸዋል።
በተለይም በቅርቡ የጀመርናቸው የገጠር ኮሪደር ሥራዎች የገጠር የመኖሪያ ከባቢዎችን እንደገና በማደስ የነዋሪዎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል ያለሙ ናቸው ብለዋል።
የኮሪደር ልማት ሥራ ወደ ከተማው ጫፎች እንዲደርስ ሀብት በማሰባሰብ የከወኑትን የአዲስ አበባ አስተዳደር እና የክፍለ ከተማ አመራሮችን ከልብ ለማመስገን እፈልጋለሁ ብለዋል።
በከተማችን የሚገኙ ሌሎች ክፍለ ከተሞች እና በመላው ሀገራችን የሚገኙ ከተሞችም የከተማ አኗኗርን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ በአዲስ ምናብ እና የሀሳብ ውቅር ለመሥራት በተነሳንበት በአሁኑ ወቅት ዜጋ ተኮር የሆኑ ተግባራትን ቅድሚያ ሰጥተው መሥራታቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቀርባለሁ ነው ያሉት።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025