
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2017(ኢዜአ)፦ የአንበሳ ጋራዥ-ጃክሮስ-ጎሮ አደባባይ የኮሪደር ሥራ ከፍተኛ የፍሰት ጭንቅንቅ የነበረበትን ከባቢ ቀይሮታል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት የእግረኛ መንገዶች፣ የብስክሌት መንገዶች፣ የመኪና ማቆሚያዎች፣ የሕፃናት መጫወቻዎች፣ ሱቆች፣ የሕዝብ ማረፊያ ፕላዛዎች፣ የሕዝብ መጸዳጃዎች፣ የተለዩ የታክሲ እና የአውቶቡስ ቤዮች መሠራት አካባቢውን የበለጠ ተደራሽ፣ አካታች እና ለመኖር ምቹ አድርጎ እንደገና የገነባ ተግባር ነው ብለዋል።
የከተማም ሆነ የገጠር ኮሪደር ሥራዎች የከበረ የሰውልጅ የአኗኗር ዘይቤን ያስተዋወቀ እና ፍትኃዊ የሕዝባዊ ስፍራዎች አጠቃቀምን በመፍጠርም ማኅበረሰቦችን ከፍ ያደረገ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

በተለይም በቅርቡ የጀመርናቸው የገጠር ኮሪደር ሥራዎች የገጠር የመኖሪያ ከባቢዎችን እንደገና በማደስ የነዋሪዎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል ያለሙ ናቸው ብለዋል።
የኮሪደር ልማት ሥራ ወደ ከተማው ጫፎች እንዲደርስ ሀብት በማሰባሰብ የከወኑትን የአዲስ አበባ አስተዳደር እና የክፍለ ከተማ አመራሮችን ከልብ ለማመስገን እፈልጋለሁ ብለዋል።

በከተማችን የሚገኙ ሌሎች ክፍለ ከተሞች እና በመላው ሀገራችን የሚገኙ ከተሞችም የከተማ አኗኗርን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ በአዲስ ምናብ እና የሀሳብ ውቅር ለመሥራት በተነሳንበት በአሁኑ ወቅት ዜጋ ተኮር የሆኑ ተግባራትን ቅድሚያ ሰጥተው መሥራታቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቀርባለሁ ነው ያሉት።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026