
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2017(ኢዜአ)፦ የአንበሳ ጋራዥ-ጃክሮስ-ጎሮ አደባባይ የኮሪደር ሥራ ከፍተኛ የፍሰት ጭንቅንቅ የነበረበትን ከባቢ ቀይሮታል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት የእግረኛ መንገዶች፣ የብስክሌት መንገዶች፣ የመኪና ማቆሚያዎች፣ የሕፃናት መጫወቻዎች፣ ሱቆች፣ የሕዝብ ማረፊያ ፕላዛዎች፣ የሕዝብ መጸዳጃዎች፣ የተለዩ የታክሲ እና የአውቶቡስ ቤዮች መሠራት አካባቢውን የበለጠ ተደራሽ፣ አካታች እና ለመኖር ምቹ አድርጎ እንደገና የገነባ ተግባር ነው ብለዋል።
የከተማም ሆነ የገጠር ኮሪደር ሥራዎች የከበረ የሰውልጅ የአኗኗር ዘይቤን ያስተዋወቀ እና ፍትኃዊ የሕዝባዊ ስፍራዎች አጠቃቀምን በመፍጠርም ማኅበረሰቦችን ከፍ ያደረገ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

በተለይም በቅርቡ የጀመርናቸው የገጠር ኮሪደር ሥራዎች የገጠር የመኖሪያ ከባቢዎችን እንደገና በማደስ የነዋሪዎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል ያለሙ ናቸው ብለዋል።
የኮሪደር ልማት ሥራ ወደ ከተማው ጫፎች እንዲደርስ ሀብት በማሰባሰብ የከወኑትን የአዲስ አበባ አስተዳደር እና የክፍለ ከተማ አመራሮችን ከልብ ለማመስገን እፈልጋለሁ ብለዋል።

በከተማችን የሚገኙ ሌሎች ክፍለ ከተሞች እና በመላው ሀገራችን የሚገኙ ከተሞችም የከተማ አኗኗርን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ በአዲስ ምናብ እና የሀሳብ ውቅር ለመሥራት በተነሳንበት በአሁኑ ወቅት ዜጋ ተኮር የሆኑ ተግባራትን ቅድሚያ ሰጥተው መሥራታቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቀርባለሁ ነው ያሉት።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026