
አዳማ ፤ሰኔ 4/2017(ኢዜአ)፡- በጣና ሃይቅ ላይ የትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠትና የቱሪዝም ፍሰቱን ለማሳደግ ታስባ ወደ አገር ውስጥ እየተጓጓዘች የምትገኘው 'ጣናነሽ 2 ጀልባ' አዳማ ከተማ ደርሳለች።
'ጣናነሽ 2' አዳማ ስትገባ የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አመራሮችና የስራ ኃላፊዎች፣ የአዳማ ከተማ ከንቲባና የከተማው ነዋሪዎች አቀባበል አድርገውላታል።
ከጂቡቲ ዶራሌህ ወደብ ተነስታ ኢትዮጵያ ጉዞ ላይ የምትገኘው 'ጣናነሽ 2' ከረጅም ጉዞ በኋላ በዛሬው ዕለት ደግሞ አዳማ ከተማ ገብታለች።

'ጣና ነሽ 2' 150 ሜትሪክ ቶን ክብደት ሲኖራት ርዝመቷም 38 ሜትር እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን ከ188 ሰው የመጫን አቅም እንዳላትም ተመልክቷል።
የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ በተለያዩ ሐይቆች ላይ በዘመናዊ ጀልባዎች የታገዘ የውኃ ላይ ትራንስፖርት ለመስጠት ጥረት እየተደረገ መሆኑን መግለጹ ይታወሳል።
ለዚህም የሚያግዙ ዘመናዊ ጀልባዎችን በማስመጣት በሀገር ውስጥ ሐይቆች ላይ ትራንስፖርትን ተደራሽ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው፣ 'ጣና ነሽ 2' ለዚሁ አገልግሎት ወደ መዳረሻዋ ባህር ዳር እየተጓጓዘች መሆኑን ተቋሙ አመልክቷል።
ወደፊትም ላንጋኖ እና ሻላን ጨምሮ በሁሉም ሐይቆች ላይ በዘመናዊ ጀልባዎች የታገዘ የውኃ ላይ ትራንስፖርት ለመስጠት እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን መዘገባችን ይታወሳል።
የ'ጣና ነሽ 2' ጉዞ የተሳለጠ እንዲሆን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እና የየክልሎቹ የትራፊክ ፖሊስ አባላት የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከቱ እንደሆነም ተገልጿል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጀልባዋን ለማሳለፍ በመንገድ ላይ ያሉ የኤሌክትሪክ ገመዶችን በማንሳት እንዲሁም የሚቋረጡ የኤሌክትሪክ አገልግሎቶችን በፍጥነት በመመለስ ርብርብ እያደረጉ መሆኑም ተመልክቷል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026