የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በአዲስ አበባ የተከናወኑ የልማት ስራዎች ወጣቶችን በዘላቂነት ተጠቃሚ የሚያደርጉ ናቸው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Jun 12, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 4/2017(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ከተማ የተከናወኑ የልማት ስራዎች የወጣቶችን ተጠቃሚነት በዘላቂነት የሚያረጋግጡ መሆናቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ።


ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከሁሉም ክፍለ ከተሞች ከተውጣጡ የመዲናዋ ወጣቶች ጋር "የወጣቶች ሚና ለሁለንተናዊ ብልጽግና" በሚል መሪ ሀሳብ ውይይት አካሂደዋል።


ከንቲባዋ በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ወጣቶች የሀገር ጉልበትና ተስፋ ናቸው ብለዋል።


መንግስት በምጣኔ ሃብት ያደገችና ለዜጎች ምቹ ሀገርን ለመፍጠር በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸው በዚህ ውስጥ የወጣቶች ሚና ወሳኝ እንደሆነ ጠቅሰዋል።


በከተማዋ በሚከናወኑ የልማት ስራዎች፣ በሀገራዊ ፕሮጀክቶችና በዘላቂ ሰላም ግንባታ ሂደት ወጣቶች ጉልህ ሚና እየተጫወቱ እንደሚገኙ ተናግረዋል።


የአሁኑ ትውልድ በሀገራዊ ግዙፍ ፕሮጀክቶች፣ በአረንጓዴ አሻራ፣ በከተማ ልማት፣ በምግብ ራስን ለመቻልና በሌሎች የልማት ሥራዎች ታሪክ እየሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።


ወጣቶች በሰው ተኮር፣ በበጎ ፈቃድ፣ ሰላምና ጸጥታ፣ በኮሪደር ልማትና ሌሎች ፕሮጀክቶች ጉልህ ሚና በመጫወት የስራ እድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።


በውይይት መድረኩ የተሳተፉ ወጣቶች በበኩላቸው በከተማዋ በስራ እድል ፈጠራ፣ በፖለቲካ ተሳትፎ፣ በስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፣ በወጣት ማእከላት ተጠቃሚ መሆናቸውን አንስተዋል።


ወጣቶችን በፖለቲካ፣ በማህበራዊና ምጣኔ ሃብት ዘርፎች ተሳታፊና ተጠቃሚ በማድረግ አካታች እድገት ለማምጣት የተጀመረው ተግባር የሚበረታታና ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት መሆኑን ገልጸዋል።


የስራ እድል ፈጠራ፣ የብድር አቅርቦት፣ የመስሪያ ቦታ፣ የሰብዕና መገንቢያ ማዕከላት፣ አማራጭ የቤት አቅርቦትን በተመለከተ ጥያቄዎችን አቅርበዋል።


የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ በላይ ደጀን፥ ወጣቶች ያነሷቸው ሀሳቦችና ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ እንደሚፈቱ ተናግረዋል።


ባለፉት የለውጥ ዓመታትም ለወጣቶች በርካታ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መገንባታቸውን ገልጸዋል።


በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ጥራቱ በየነ፥ የወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ ትልቅ ትኩረት የተሰጠው መሆኑን አስረድተዋል።


ባለፉት አሥር ወራት ብቻ 301ሺህ ወጣቶች የስራ እድል እንደተፈጠረላቸው ገልጸው፥ በኢንተርፕራይዝ ለተደራጁ ወጣቶች ደግሞ 2 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ብድር መሰጠቱን ተናግረዋል።


ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማጠቃለያ መልዕክታቸው በከተማዋ በተገነቡ 114 የወጣት ስብዕና መገንቢያ ማዕከላት አማካኝነት ወጣቱን አምራች ዜጋ ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎችን የማስፋት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።


ወጣቶቹ በስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፣ በወንዝ ዳርቻ፣ በኮሪደር ልማትና በመኪና ማቆሚያዎች በተከናወኑ የልማት ስራዎች በፈጠራ በመታገዝ በዘላቂነት የስራ እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከተማ አስተዳደሩ ቁርጠኛ ነው ብለዋል።


በምጣኔ ሃብት፣ በፖለቲካና በማህበራዊ ዘርፎች የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።


ወጣቶች በክህሎትና በእውቀት ተወዳዳሪ በመሆን ለሀገር ብልፅግና በትጋት መስራት እንደሚገባቸውም አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026