የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የኮሪደር ልማቱ ለንግድ ስርዓቱ መሳለጥ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል

Jun 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 5/2017(ኢዜአ)፦በመዲናዋ በመከናወን ላይ ያለው የኮሪደር ልማት ለንግድ ስርዓቱ መሳለጥ ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ተጠቃሚ እንዳደረጋቸው የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ተናገሩ፡፡

አዲስ አበባ የአፍሪካ መዲና፣ የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽንና የአለም የዲፕሎማቲክ ማዕከል መሆኗን ተከትሎ በርካታ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች ይከናወኑባታል፡፡

አዲስ አበባን በስሟ ልክ ውብ በማድረግ፣ አለም አቀፍ ተወዳዳሪነቷን የሚመጥን ቁመና ለማላበስና ለነዋሪቿ ምቹ ለማድረግ የተከናወኑ የልማት ስራዎች የሚታይ ውበትና ለውጥ አምጥተዋል፡፡


የሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት አካል የሆነው የአንበሳ ጋራዥ፣ ጃክሮስ ፣ የጎሮ አደባባይ ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ የዚሁ ማሳያ ነው፡፡

ከአንበሳ ጋራዥ እስከ ጎሮ አደባባይ በተሰራው የኮሪደር ልማት ዙሪያ በንግድ ስራ የተሰማሩ ግለሰቦች ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንዳሉት የኮሪደር ልማቱ ምቹ የስራ ሁኔታን ፈጥሮላቸዋል።

የኮሪደር ልማቱ አስፈላጊ፣ ወቅቱን የዋጀ እና ለሌሎች ከተሞች በምሳሌነት የሚወሰድ መሆኑንም ነው የጠቀሱት።

በሴቶች አልባሳትና ኮስሞቲክስ መሸጫ ሱቅ የምትሰራው ወጣት እየሩሳሌም ፀጋዬ ካሁን ቀደም መንገዱ ጠባብ ከመሆኑ ባለፈ ቤቶቹ በቆርቆሮና በሸራ የተሰሩ ስለነበሩ ለንግድ እንቅስቃሴ አስቸጋሪ እንደነበሩ ነው የገለፀችው።


የካፌ ባለቤት የሆኑት አቶ አዳነ በሪሁን በሰፈሩ ለረጅም አመታት መስራታቸውን ገልፀው ቀደም ሲል በአካባቢው የፍሳሽ ማስወገጃ ስላልነበር ስራቸውን አስቸጋሪ አድርጎባቸው እንደነበረ አስታውሰዋል።

የየረር ፋርማሲ ባለቤት ወይዘሮ አስቴር አድማሱ እንዳሉት የትራፊክ መጨናነቅና የተበላሹ መንገዶች በንግድ እንቅስቃሴያቸው ላይ ከፍተኛ ጫና ሲያሳድሩ ቆይተዋል።


የኮሪደር ልማቱ ይህን ችግር በመፍታት ምቹ የመንቀሳቀሻ ስፍራ በመፍጠር ሸቀጦችን እንደልብ ከቦታ ቦታ ለማዘዋወር የሚረዳ እንደሆነ እምነታቸውን ገልጸዋል።

በአዋቂዎች አልባሳት ሽያጭ የተሰማሩት አቶ ሀይረዲን ሱልጣን በበኩላቸው ቦታው ካሁን ቀደም ለስራ የማይመች፣ አስቸጋሪና የተጨናነቀ እንደነበር አስታውሰው ለውጡ ከፍተኛ መሆኑን ነው የገለፁት።

የኮሪደር ልማቱ ለከተማዋ ነዋሪ መሰረታዊ ለውጥ ማምጣቱን በመናገር የመኪና እና የእግረኛ መንገዶች ስፋትና ውበት አካባቢውን በብዙ መልኩ የለወጠና ነዋሪውን ያስደሰተ መሆኑን ነጋዴዎቹ ገልፀዋል።


በመዲናዋ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ከተማዋን ውብ ከማድረጉ ባለፈ የንግድ ስርዓቱን በማሳለጥ የንግዱ ማህበረሰብ ተጠቃሚ እንዲሆን ማድረጉን ወጣት እየሩሳሌም ፀጋዬ ፣ አቶ አዳነ በሪሁን እና ወይዘሮ አስቴር አድማሱ አንስተዋል።



በተለይም በንግድ ስራ የተሰማሩ አካላት እስከ ምሽቱ አራት ሰአት ድረስ እንዲሰሩ መደረጉ አዲስ የስራ ባህልን ለማዳበር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ አቶ ነስሩ ሱልጣንና አቶ ሀይረዲን ሱልጣን ተናግረዋል፡፡።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026