የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር የተገነባው የሶላር ሀይል ማመንጫ አቅርቦትን ማሳደግ የሚያስችል ማሳያ ፕሮጀክት ነው

Jun 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሰኔ 5/2017 (ኢዜአ)፦በውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር የተገነባው ሶላር ፕሮጀክት ለተቋሙ ሀይልን ከማቅረብ በዘለለ የሶላር ሀይልን አመንጭቶ ወደ ዋናው ግሪድ የሚያስገባ ማሳያ ፕሮጀክት ነው ሲሉ የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር 100 ኪሎ ዋት የሚያመነጭ የመጀመሪያውን የሶላር ፕሮጀክት በተቋሙ ጊቢ ውስጥ አስመርቆ ለአገልግሎት አብቅቷል፡፡


የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ፕሮጀክቱን መርቀው ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት በአገሪቱ የሀይል ማመንጨት አቅምን ለማሳደግ በርካታ ተግባራትን በትኩረት እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡

በዚህም በአገሪቱ ስድስት ነጥብ ስምንት ጊጋ ዋት ሀይል የማመንጨት አቅም ላይ መድረስ የተቻለ ሲሆን ከሶላር ኢነርጂ ወደ 10ሺ የሚጠጋ ሃይል በማመንጨት ማህበረሰብን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል፡፡

የሀይል አቅርቦትን ከማሳደግ አንጻር ውጤታማ ተግባራት መከናወኑን ያነሱት ሚኒስትሩ በቀጣይም የሀይል አቅርቦትን የማሳደግ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

በሚኒስቴሩ ግቢ ውስጥ የተገነባው 100 ኪሎ ዋት የሚያመነጭ የሶላር ፕሮጀክት የሶላር ኢነርጂን በከተማ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚቻል ማሳያ መሆኑንም አስታውቀዋል።

የተገነባው ሶላር ፕሮጀክት ተቋሙ የሚፈልገውን ሀይል ተጠቅሞ ቀሪውን ወደ ዋናው ግሪድ የሚያስገባና ሌሎች ሊከተሉት የሚገባ ምሳሌ የሚሆን ፕሮጀክት ነው ብለዋል፡፡

በተለይ ባለሀብቶች የተለያዩ ተቋማት የውሀ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር የጀመረውን ተሞክሮ በመውሰድ ተግባራዊ ቢያደርጉ ለሀይል አቅርቦት ማደግ የሚኖረው ጠቀሜታ የጎላ መሆኑንም አመላክተዋል።


የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) በበኩላቸው ኢትዮጵያ ከፍተኛ የታዳሽ ሀይል ማመንጨት የሚችል እምቅ አቅም እንዳላት አስታውቀዋል፡፡

ይህን አቅም በአግባቡ ለመጠቀም የሚያስችሉ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አንስተው፤ በዚህም በገጠር አካባቢዎች፣ በጤና ተቋማትና በትምህርት ቤቶች ያለውን የመብራት ሀይል ተጠቃሚነት ማሳደግ መቻሉን ተናግረዋል፡፡

መሰል የሶላር ኢነርጂ ፕሮጀክቶችን የተለያዩ ተቋማት እና ግለሰቦች ቢጠቀሙ የአገሪቱን ኢነርጂ ፍጆታ መሸፈን የሚያስችል በመሆኑ በቀጣይ ሊሰራበት ይገባልም ብለዋል።

በቀጣይ ተቋማት የሶላር ኢነርጂ እንዲጠቀሙ ግንዛቤ መፍጠር እንዲሁም በህግ በማስደገፍ ወደ ስራ ማስገባት እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡

የተገነባው የሶላር ኢነርጂ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከዓለም አቀፍ ሶላር አልያንስ ጋር በመተባበር እንደሆነም ተመላክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026