የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ቋሚ ኤግዚቢሽኑ የነገዋን ኢትዮጵያ የምንሰራበት ትልቅ ሀብት የያዘ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

Jun 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 7/2017(ኢዜአ)፦ የሳይንስ ሙዚየም ቋሚ ኤግዚቢሽን የነገዋን ኢትዮጵያ የምንሰራበት እና የምንገነባበት ትልቅ ሀብት የያዘ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

ኤግዚቢሽኑ ልጆች የነገ ማንነታቸው እንዲሰራ እና የነገ መሻታቸው እውን እንዲሆን የሚያደርግ ነውም ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት የሳይንስ ሙዚየም ቋሚ ኤግዚቢሽን ክፍል ዛሬ በይፋ ተከፍቷል።


ኤግዚቢሽኑ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና የኢትዮጵያ ምላሽ፣ ግብርና፣ የውኃ ኃይል እና ኢነርጂ፣ ኤሮኖቲክስ እና አቪየሽን ላይ ያተኮሩ አምስት የዐውደ ርዕይ ምድቦችን የያዘ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሳይንስ ሙዚየም ሕንጻ ከሁለት ዓመት ገደማ በፊት ተገንብቶ በጊዜያዊ ኤግዚቢሽን መመረቁን አስታውሰዋል።

ቋሚ ኤግዚቢሽኑ ከፍተኛ ሀብት መጠየቁን ጠቁመው በጣም ጠቃሚ ነገር የያዘ መሆኑንና ነገን የምንሰራበት ሙዚየም እዚህ ነው ያለው ሲሉ ገልጸዋል።

ኢትዮጵያውያን ነገን መስራት ነገን መለወጥ ከፈለጉ ልጆቻቸውን ወደ ኤግዚቢሽኑ ስፍራ ሊያመጧቸው እንደሚገባም አመልክተዋል።


ልጆች በሙዚየሙ ያሉ ነገሮችን በተግባር በማየት የነገ ማንነታቸውን መስራት እና የነገ መሻታቸውን እውን ማድረግ ይችላሉ ሲሉም ገልጸዋል።

ኤግዝቢሽኑ ለልጆች ታላቅ በረከት ይዞ መጥቷል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ልጆች ቴክኖሎጂን በሚገባ እንዲጠቀስሙ እና አልፎም ፈጣሪ እንዲሆኑ በር የሚከፍት ነው ብለዋል።

ወላጆች ቋሚ ኤግዚቢሽኑ ለልጆች ትልቅ ዕድል መሆኑን ተገንዝበው ወደ ስፍራው ይዘዋቸው እንዲመጡ እና መልካም ዘርን እንዲዘሩባቸው አስገንዝበዋል።

ይህንን እያየ ያደገ ልጅ ጥበብ እና እውቀትን በማዳበር ነገ ሀገሩን የሚጠብቅ፣ ሀገር የሚያበለጽግ፣ ሀገር የሚያለማ እና ሀገር የሚያጸና ይሆናል ሲሉም ተናግረዋል።

በተጨማሪም መምህራን፣ ተመራማሪዎችና ነገን መስራት የሚፈልጉ ሰዎች በሙሉ ኤግዚቢሽኑን እንዲጎበኙ ጥሪ አስተላልፈዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለቋሚ ኤግዚቢሽኑ ግንባታ ድጋፍ ላደረጉ ሀገራት እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ምስጋና አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025