የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ቋሚ ኤግዚቢሽኑ የነገዋን ኢትዮጵያ የምንሰራበት ትልቅ ሀብት የያዘ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

Jun 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 7/2017(ኢዜአ)፦ የሳይንስ ሙዚየም ቋሚ ኤግዚቢሽን የነገዋን ኢትዮጵያ የምንሰራበት እና የምንገነባበት ትልቅ ሀብት የያዘ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

ኤግዚቢሽኑ ልጆች የነገ ማንነታቸው እንዲሰራ እና የነገ መሻታቸው እውን እንዲሆን የሚያደርግ ነውም ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት የሳይንስ ሙዚየም ቋሚ ኤግዚቢሽን ክፍል ዛሬ በይፋ ተከፍቷል።


ኤግዚቢሽኑ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና የኢትዮጵያ ምላሽ፣ ግብርና፣ የውኃ ኃይል እና ኢነርጂ፣ ኤሮኖቲክስ እና አቪየሽን ላይ ያተኮሩ አምስት የዐውደ ርዕይ ምድቦችን የያዘ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሳይንስ ሙዚየም ሕንጻ ከሁለት ዓመት ገደማ በፊት ተገንብቶ በጊዜያዊ ኤግዚቢሽን መመረቁን አስታውሰዋል።

ቋሚ ኤግዚቢሽኑ ከፍተኛ ሀብት መጠየቁን ጠቁመው በጣም ጠቃሚ ነገር የያዘ መሆኑንና ነገን የምንሰራበት ሙዚየም እዚህ ነው ያለው ሲሉ ገልጸዋል።

ኢትዮጵያውያን ነገን መስራት ነገን መለወጥ ከፈለጉ ልጆቻቸውን ወደ ኤግዚቢሽኑ ስፍራ ሊያመጧቸው እንደሚገባም አመልክተዋል።


ልጆች በሙዚየሙ ያሉ ነገሮችን በተግባር በማየት የነገ ማንነታቸውን መስራት እና የነገ መሻታቸውን እውን ማድረግ ይችላሉ ሲሉም ገልጸዋል።

ኤግዝቢሽኑ ለልጆች ታላቅ በረከት ይዞ መጥቷል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ልጆች ቴክኖሎጂን በሚገባ እንዲጠቀስሙ እና አልፎም ፈጣሪ እንዲሆኑ በር የሚከፍት ነው ብለዋል።

ወላጆች ቋሚ ኤግዚቢሽኑ ለልጆች ትልቅ ዕድል መሆኑን ተገንዝበው ወደ ስፍራው ይዘዋቸው እንዲመጡ እና መልካም ዘርን እንዲዘሩባቸው አስገንዝበዋል።

ይህንን እያየ ያደገ ልጅ ጥበብ እና እውቀትን በማዳበር ነገ ሀገሩን የሚጠብቅ፣ ሀገር የሚያበለጽግ፣ ሀገር የሚያለማ እና ሀገር የሚያጸና ይሆናል ሲሉም ተናግረዋል።

በተጨማሪም መምህራን፣ ተመራማሪዎችና ነገን መስራት የሚፈልጉ ሰዎች በሙሉ ኤግዚቢሽኑን እንዲጎበኙ ጥሪ አስተላልፈዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለቋሚ ኤግዚቢሽኑ ግንባታ ድጋፍ ላደረጉ ሀገራት እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ምስጋና አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026