የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ኢትዮጵያን ለመገንባት ፉክክር ብቻ በቂ አይደለም ትብብር ያስፈልጋል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

Jun 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 12/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያን ለመገንባት ፉክክር ብቻ በቂ አይደለም ትብብር ያስፈልጋል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከመላው ኢትዮጵያ ከተውጣጡ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ጋር ውይይት አድርገዋል።

ውይይቱ የፖለቲካ ምህዳሩ ለውጥ አካል መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፓርቲዎች ሰብሰብ ብለው ጠንክረው እና ሀሳብ ኖሯቸው ከመጡ ከሚፎካከሩን ጋር በትብብር ለመስራት በራችን ክፍተ ነው ብለዋል።

ለዚህ ዋናው መስፈርቱ ግን ኢትዮጵያ አንድ ታላቅ ሀገር ሆና እንድትቀጥል በመንግስትም ሆነ በተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በኩል በተሰወነ ደረጃ የመተው ልምምድ ያስፈልጋል ነው ያሉት።


በካቢኔ አባልነት አብረውን እየሰሩ ያሉ የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ማክሮ ኢኮኖሚን ጨምሮ በበርካታ አጀንዳዎች ላይ በመከራከርም በመቃረንም ሆነ በመጠየቅ አብረን ስንሰራ አራት ዓመታት ሆነውናል ብለዋል።

እንዲህ አይነት የትብብር ልምምድ ካላካበትን በጋራ ሀገር ልንሰራ ስለማንችል ይህም ከውጊያው እና ከስደቱ ስለሚሻል ነው አብረን እየሰራን ያለነው ሲሉም ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለጹት።

ለዚህ ነው ፉክክር ብቻ በቂ አይደለም ትብብር ያስፈልጋል የምንለው ባንግባባ እንኳን እየተባበርን ኢትዮጵያን ብንገነባ ይሻላል የሚል ሀሳብ አለን ሲሉም አክለዋል።

ይህንንም ተናግረናል ጽፈናል ደግሞም ልንኖረው እየሞከርን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ይህም ሙሉ ካልሆነ እናሰፋዋለን ብለዋል።

ነገር ግን ከዲሞክራሲ ልምምድ ችግር የተነሳ በየቦታው ውስንነቶች እንደሚኖሩ ጠቁመው ለውጡን እያየን የጎደለውን እየሞላን ብንሄድ የተሻለ ሀገር ለመፍጠር ያግዛል ነው ያሉት።


ቀደም ሲል በነበረን ውይይት በዞን እና በወረዳ ደረጃ ችግር እየገጠማችሁ እንደሆነ ባነሳችሁት መሰረት ከሁሉም ክልሎች ጋር በመነጋገር ሁሉም ዞኖች እንዲያነጋግሯችሁ ተደርጎ ከሰላሳ በላይ ጉዳዮች መቀረፋቸውን ገልጸዋል።

እንዲሁም እስከ ዞን ድረስ ባለው መዋቅር የሚገጥሟችሁን ችግሮች ለመፍታት ምርጫ ቦርድ የመንግስትን ተሳትፎ ሲጠይቅ ከፍተኛ የስራ ሀላፈዎችን እየመደበ እንዲጣራ እያደረገ ያለው ጉዳዩ እንዳይታፈን ስለምንፈልግ ጭምር ነውም ሲሉም ተናግረዋል።

በጎደለው ደግሞ እንዲህ ስንገናኝ ግብዓት እየወሰድን እያረምን ለመሄድ ነው ያለው ፍላጎት ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደፓርቲ ውስጣችንንም በየጊዜው እየገመገምን እያረምን የምንሄደው ለዚሁ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026