
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2017(ኢዜአ)፥ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውና የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የቆዳ ኢንዱስትሪው እንዲነቃቃ ማድረጉን የቆዳ ኢንዱስትሪ ምርምርና ልማት ማዕከል አስታወቀ።
የቆዳ ኢንዱስትሪ ምርምርና ልማት ማዕከል ስራ አስኪያጅ አቶ ዙልፍካር አባጅሐድ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በንቅናቄው በተለያዩ ምክንያቶች ስራ አቁመው የቆዩ ስድስት ኩባንያዎች በተደረገላቸው ድጋፎች ወደ ምርትና ውጭ መላክ ስራዎች ተመልሰዋል።
የተኪ ምርት ስትራቴጂ ተዘጋጅቶ በመተገብሩም ለጸጥታ አካላትና ለተለያዩ ተቋማት ለስራ የሚውሉ ከቆዳ የሚዘጋጁ ጫማዎች ሙሉ ለሙሉ በአገር ውስጥ አምራቾች እየቀረበ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በ2017 በጀት ዓመት አስራ አንድ ወራት ብቻ 196 ሚሊዮን ዶላር ግምት ያለው የቆዳ ምርት በአገር ውስጥ በማምረት ከውጭ የሚገባውን መተካት መቻሉን ገልፀዋል።
የአገር ውስጥ የቆዳ ምርቶች ጥራት፣ ዲዛይንና ስብጥር በመሻሻሉ የማህበረሰቡ አመለካከትና አጠቃቀም እያደገ መምጣቱን ተናግረው በመዲናዋ የሚዘጋጁ አለም አቀፍ ሁነቶች የቆዳ ውጤቶችን ለማስተዋወቅና የገበያ ትስስር ለመፍጠር ጉልህ ሚና እየተጫወቱ ነው ብለዋል።
የጥሬ ቆዳና ሌጦ የጥራት ችግሮችን ለመፍታት ከእርድ ጀምሮ እስከ ፋብሪካ ድረስ ያሉ ተዋናዮች ላይ የሚታዩ የክህሎት ክፍተቶች ላይ ያተኮሩ ስልጠናዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን ተናግረዋል።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ወደተሟላ ትግበራ ከመግባቱ በፊት ለቆዳ ምርት አስፈላጊ ኬሚካሎችን ከውጭ ለማስገባት የውጭ ምንዛሬ ተግዳሮት እንደነበረ አውስተዋል።
አሁን ላይ ማሻሻያው ተግባራዊ በመሆኑ የውጭ ምንዛሬ አቅርቦት በመሻሻሉ ግብአቱን ከውጭ ለማስገባት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል ብለዋል።
የቆዳ ፋብሪካዎች ከውሃ ፣ከኬሚካልና ሌሎች ሀብቶች አጠቃቀም፣ ከሠራተኞች አያያዝና ደህንነት መጠበቅና ሌሎች መስፈርቶች አንጻር ማሟላት ያለባቸው አለም አቀፍ መስፈርቶች እንዳሉ ተናግረዋል።
‘ሌዘር ወርኪንግ ግሩፕ’ የተሰኘ አለም አቀፍ ድርጅት በየዓመቱ የቆዳ ፋብሪካዎችን ኦዲት በማድረግ የብቃት ማረጋገጫ ይሰጣል ብለዋል።
ቀደም ሲል በኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ማረጋገጫውን ያገኘ ድርጅት እንዳልነበረ ገልጸው፤ በቅርቡ ሰባት የቆዳ ፋብሪካዎች በተደረገላቸው ድጋፍ የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት አግኝተዋል ነው ያሉት።
ይህም በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የሚያስችላቸው መሆኑን ገልጸዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026