
አዲስ አበባ፤ሰኔ 16/2017 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ የገበያ ማዕከላት መስፋፋት ምርቶችን በበቂ እና በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘት እያስቻላቸው መሆኑን ኢዜአ ያነጋገራቸው ሸማቾች ገለጹ።

በመዲናዋ የተገነቡ የገበያ ማዕከላት አምራቹንና ሸማቹን እንደ ድልድይ ሆኖ በቀጥታ በማገናኘት የኑሮ ውድነቱን እና የዋጋ ንረትን በመቀነስ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው፡፡
ለማሳያነትም ኢዜአ ከእነዚህ ማዕከላት አንዱ በሆነው የንፋስ ስልክ ላፍቶ ቁጥር ሁለት ሁለገብ የገበያ ማዕከልን እንቅስቃሴ ቅኝት አድርጓል።
ሸማቾች እንደሚሉትም በማዕከሉ በተመጣጣኝ ዋጋ የአትክልትና ፍራፍሬ እና የሰብል ምርቶችን እየገዙ እና እየተጠቀሙ መሆኑን አንስተዋል።
በማዕከሉ ስትገበያይ ያገኘናት ሸማች አበበች አሰፋ እንደገለጸችው ፤ በማዕከሉ ሁሉንም አይነት አትክልትና ፍራፍሬ በተመጣጣኝ ዋጋ እየሸመተች መሆኑን በመግለጽ፤ በዋጋ ተመጣጣኝ የሆነ አገልግሎት እንዳገኘች ትናገራለች፡፡
ሌላው ያነጋገርነው ሸማች ተማም ጀማል በበኩሉ፤ ለእኛ ለሸማቾች መንግስት በየአቅራቢያችን በገነባቸው ማዕከላት አትክልትና ፍራፍሬዎችና የሰብል ምርቶችን በአቅራቢያችን በተመጣጣኝ ዋጋ መግዛት መቻላችን እፎይታ ሰጥቶናል ነው ያለው፡፡

የማዕከሉ መኖር ውጪ ላይ ካለው ገበያ ሰፊ ልዩነት እንዳለውና አቅማችንን ባማከለ ዋጋ እየተገበያየን ነው ያለችው ደግሞ የምስራች አባይነህ ናት፡፡

በማዕከሉ ያነጋገርናቸው አምራቾች መካከል አቶ ተስፉ ወጂ እንዳሉት፤የገበያ ማእከላት መኖራቸው የግብይቱን ሰንሰለት በማሳጠር ምርቶቻቸውን ለተጠቃሚ ለማድረስ እድል የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የሰብል ምርቶችን ጤፍ ከ10ሺህ ብር ጀምሮ፣ ሽንኩርት ከ35 ብር ጀምሮ በመሸጥ በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እየሸጡ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
ሌላው ያነጋገርናቸው አምራች አቶ ደረጄ ጋሪ በበኩላቸው ምርቶችን ውጭ ካለው ገበያ እስከ ሃያ ፐርሰንት ቅናሽ ለህብረተሰቡ እያቀረቡ መሆኑን ነው የገለጹት፡፡

በላፍቶ ቁጥር ሁለት ሁለገብ የገበያ ማዕከል ዋና ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ከማል ሃጂ ሰኢድ እንዳሉት ፤ የገበያ ማዕከሉ መገንባት ለሸማችና ለአምራቹ ግንኙነት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ ነው፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ምክትል ሀላፊ ፍስሀ ጥበቡ ቢሮው ገበያ ለማረጋጋት የቅዳሜና እሁድን ጨምሮ ከሁሉም የሃገሪቱ አካባቢዎች ምርቶች እንዲገቡ እያደረገ እንደሚገኝ አመልክተዋል፡፡

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026