የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በቱሪዝም ዘርፍ የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለመጨመር በቴክኖሎጂ የተደገፈ የመረጃ ስርዓት ማስፋት ይገባል

Jun 24, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሰኔ 16/2017 (ኢዜአ)፦በቱሪዝም ዘርፍ የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለመጨመር በቴክኖሎጂ የተደገፈ የመረጃ ስርዓት ማስፋት ይገባል ሲሉ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ ተናገሩ።

በኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን የተዘጋጀውና ትኩረቱን ቱሪዝምና ቴክኖሎጂ ላይ ያደረገ ፎረም በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።

የቱሪዝም ሚኒስትሯ ሰላማዊት ካሳ በመርሀ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ዋና ዋና የኢኮኖሚ ምንጭ ተብለው ከተለዩ ዘርፎች መካከል ቱሪዝም አንዱ መሆኑን አንስተዋል።

ኢትዮጵያ በርካታ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ሀብቶችና ባህላዊ እሴቶች ቢኖሯትም ከዘርፉ የሚገኘው ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እምብዛም ሆኖ ቆይቷል።


ይሁን እንጂ የለውጡ መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ልዩ ትኩረት አዳዲስ መዳረሻዎችን የማልማት፣ ነባሮችን የማደስና ዘርፉን የማዘመን ስራዎች ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል ነው ያሉት።

በዚህም ትርጉም ያለው ለውጥ በማምጣት አበረታች ውጤት እንዲመዘገብ አስቻይ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል።

ዘርፉ ከሚያስገኘው ጠቀሜታና ካለው እምቅ ሀብት አኳያ አሁንም ብዙ ስራዎች ያስፈልጋል ሲሉ ሚኒስትሯ ገልጸዋል።

በተለይም በቴክኖሎጂ የተደገፈ የመረጃ ስርዓት በማስፋት በቱሪዝም ዘርፍ የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም መጨመር እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

እንደሀገር እየተከናወነ ያለውን ቴክኖሎጂ መር የኢኮኖሚ ግንባታ ከዳር በማድረስ በኩል የቱሪዝም ዘርፉ ከዚህም በላይ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከት ይጠበቅበታል ብለዋል።

በፎረሙ ላይ ለእይታ የቀረቡ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ለቱሪዝም ልማት ያላቸው ፋይዳ ጉልህ መሆኑን ጠቁመው በዘርፉ ተስፋ ሰጪ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ያሳያሉ ነው ያሉት።

በመሆኑም በመንግስት ከሚከናወኑ ተግባራት በዘለለ ከግሉ ዘርፍና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ከተሰማሩ አካላት ጋር በመተባበር እየተመዘገበ ያለውን ስኬት ማስቀጠል ያስፈልጋል ሲሉም ሚኒስትሯ ተናግረዋል።


የኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ነጋ ወዳጆ በበኩላቸው በክልሉ ያሉ የቱሪዝም ሀብቶችን የማስተዋወቅ ተግባራት እየተከናወኑ ስለመሆኑ ገልፀዋል።

ዛሬ በይፋ የተጀመረውና ለሁለት ቀናት የሚካሔደው ይህ ፎረም የዚሁ አካል መሆኑን በማስረዳት።

ክልሉ ለቱሪዝም ልማት ምቹ የሆኑ ስፍራዎች በብዛት ያሉበት ከመሆኑ ባሻገር የጎብኚዎችን ቀልብ የሚስቡ ባህላዊ እሴቶችና የአኗኗር ዘየዎች ያሉበት መሆኑ ደግሞ ለዘርፉ ተጨማሪ አቅም ይፈጥራል ብለዋል።

በመሆኑም የቱሪዝም ሃብቶችን የማስተዋወቅ ስራው በተገቢው መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው ለዚህም ዘመኑን የሚመጥን ቴክኖሎጂ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ነው ያሉት።

ፎረሙ በዋናነት በዘርፉ ተግባራዊ እየተደረጉ ያሉ ቴክኖሎጂዎች የሚተዋወቁበት፣ ተሞክሮ የሚቀሰምበትና ዘርፉን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያግዙ ውይይቶች የሚካሔዱበት መሆኑንም አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025