
አዲስ አበባ፤ሰኔ 16/2017 (ኢዜአ)፦በቱሪዝም ዘርፍ የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለመጨመር በቴክኖሎጂ የተደገፈ የመረጃ ስርዓት ማስፋት ይገባል ሲሉ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ ተናገሩ።
በኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን የተዘጋጀውና ትኩረቱን ቱሪዝምና ቴክኖሎጂ ላይ ያደረገ ፎረም በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።
የቱሪዝም ሚኒስትሯ ሰላማዊት ካሳ በመርሀ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ዋና ዋና የኢኮኖሚ ምንጭ ተብለው ከተለዩ ዘርፎች መካከል ቱሪዝም አንዱ መሆኑን አንስተዋል።
ኢትዮጵያ በርካታ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ሀብቶችና ባህላዊ እሴቶች ቢኖሯትም ከዘርፉ የሚገኘው ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እምብዛም ሆኖ ቆይቷል።

ይሁን እንጂ የለውጡ መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ልዩ ትኩረት አዳዲስ መዳረሻዎችን የማልማት፣ ነባሮችን የማደስና ዘርፉን የማዘመን ስራዎች ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል ነው ያሉት።
በዚህም ትርጉም ያለው ለውጥ በማምጣት አበረታች ውጤት እንዲመዘገብ አስቻይ ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል።
ዘርፉ ከሚያስገኘው ጠቀሜታና ካለው እምቅ ሀብት አኳያ አሁንም ብዙ ስራዎች ያስፈልጋል ሲሉ ሚኒስትሯ ገልጸዋል።
በተለይም በቴክኖሎጂ የተደገፈ የመረጃ ስርዓት በማስፋት በቱሪዝም ዘርፍ የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም መጨመር እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
እንደሀገር እየተከናወነ ያለውን ቴክኖሎጂ መር የኢኮኖሚ ግንባታ ከዳር በማድረስ በኩል የቱሪዝም ዘርፉ ከዚህም በላይ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከት ይጠበቅበታል ብለዋል።
በፎረሙ ላይ ለእይታ የቀረቡ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ለቱሪዝም ልማት ያላቸው ፋይዳ ጉልህ መሆኑን ጠቁመው በዘርፉ ተስፋ ሰጪ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ያሳያሉ ነው ያሉት።
በመሆኑም በመንግስት ከሚከናወኑ ተግባራት በዘለለ ከግሉ ዘርፍና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ከተሰማሩ አካላት ጋር በመተባበር እየተመዘገበ ያለውን ስኬት ማስቀጠል ያስፈልጋል ሲሉም ሚኒስትሯ ተናግረዋል።

የኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ነጋ ወዳጆ በበኩላቸው በክልሉ ያሉ የቱሪዝም ሀብቶችን የማስተዋወቅ ተግባራት እየተከናወኑ ስለመሆኑ ገልፀዋል።
ዛሬ በይፋ የተጀመረውና ለሁለት ቀናት የሚካሔደው ይህ ፎረም የዚሁ አካል መሆኑን በማስረዳት።
ክልሉ ለቱሪዝም ልማት ምቹ የሆኑ ስፍራዎች በብዛት ያሉበት ከመሆኑ ባሻገር የጎብኚዎችን ቀልብ የሚስቡ ባህላዊ እሴቶችና የአኗኗር ዘየዎች ያሉበት መሆኑ ደግሞ ለዘርፉ ተጨማሪ አቅም ይፈጥራል ብለዋል።
በመሆኑም የቱሪዝም ሃብቶችን የማስተዋወቅ ስራው በተገቢው መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው ለዚህም ዘመኑን የሚመጥን ቴክኖሎጂ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ነው ያሉት።
ፎረሙ በዋናነት በዘርፉ ተግባራዊ እየተደረጉ ያሉ ቴክኖሎጂዎች የሚተዋወቁበት፣ ተሞክሮ የሚቀሰምበትና ዘርፉን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያግዙ ውይይቶች የሚካሔዱበት መሆኑንም አብራርተዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026