
አምቦ፤ ሰኔ 19/2017 (ኢዜአ)፡-በምዕራብ ሸዋ ዞን የማር ልማት ኢኒሼቲቭን በመተግበርና የአርሶ አደሮችን ግንዛቤ በማሳደግ ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ማሳደግ መቻሉን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ተረፈ አራርሳ ለኢዜአ እንደገለጹት በዞኑ ባለፉት አሥር ወራት የተሻለ የማር ምርት ለማግኘት ታቅዶ ሲሰራ ቆይቷል።
ለእዚህም የማር ልማት ኢኒሼቲቭን ከመተግበር ባለፈ የአርሶ አደሮች ግንዛቤ በማሳደግ ምርታማነትና የልማቱን ተሳታፊዎች ተጠቃሚነት ለማሳደግ መቻሉን ነው የተናገሩት።
እንደ ሀላፊው ገለጻ አርሶ አደሮቹ ከባህላዊ ቀፎ ወደ ዘመናዊ ቆፎ ተሸጋግረው ውጤታማ እንዲሆኑ ግንዛቤያቸውን የማሳደግ ሥራ የተሰራ ሲሆን የንብ ቀፎ ድጋፍም ተደርጎላቸዋል።
በዚህም በቡድን ተደራጅተው በንብ ማነብ ሥራ ለተሰማሩ አርሶ አደሮችና ወጣቶች ከ46 ሺህ በላይ ዘመናዊ የንብ ቀፎዎች መከፋፈሉን የጠቆሙት አቶ ተረፈ በዚህም አበረታች ውጤት ተገኝቷል ብለዋል።
በልማቱ ከ24 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችና ወጣቶች የተሳተፉ ሲሆን በዚህም ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል።
ከልማቱ ተሳታፊ አርሶ አደሮች መካከል የወልመራ ወረዳ አርሶ አደር አቶ ጌታቸው ደንደና እንዳሉት በተሰጣቸው 5 ዘመናዊ ቀፎዎች በንብ ማነብ ሥራ ተሰማርተው ተጠቀሚ መሆን ችለዋል።

ልማቱን በማስፋፋት በዚህ ዓመት የቀፎዎቹን ቁጥር ወደ 22 ማሳደግ እንደቻሉ ተናግረዋል።
ከአንድ ባህላዊ ቀፎ እስከ 5 ኪሎ ግራም ማር ያገኙ የነበረው በአሁኑ ወቅት ከእያንዳንዱ ዘመናዊ ቀፎ 12 ኪሎ ግራም ማር ማግኘት መቻላቸውን ገልጸዋል።
ዘንድሮ ከ22 ዘመናዊና አንድ ባህላዊ ቀፎዎች 269 ኪሎ ግራም ማር በማግኘታቸው ሥራውን ይበልጥ ለማስፋፋት እንዳነሳሳቸውም ነው የተናገሩት፡፡
ሌላው በአምቦ ወረዳ ጎሱ ቆራ ቀበሌ የሚኖሩት አቶ ወልደሰማያት ለታ በበኩላቸው የንብ ማነብ ስራን የሚያከናውኑት ከመደበኛ እርሻ ሥራ ጐን ለጐን በመሆኑ ከዘርፉ ባገኙት ገቢ ኑሯቸው እየተሻሻለ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

ካሏቸው 38 ዘመናዊ፣ የሽግግርና ባህላዊ ቀፎዎች በዓመት ሁለት ጊዜ በማምረት ለገበያ ማቅረባቸውን ገልጸው በቀጣይ በስፋት ለማምረት እየተዘጋጁ መሆናቸው አንስተዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026