የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በዞኑ የማር ልማት ኢኒሼቲቭን በመተግበር ከዘርፉ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ተችሏል

Jun 27, 2025

IDOPRESS

አምቦ፤ ሰኔ 19/2017 (ኢዜአ)፡-በምዕራብ ሸዋ ዞን የማር ልማት ኢኒሼቲቭን በመተግበርና የአርሶ አደሮችን ግንዛቤ በማሳደግ ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ማሳደግ መቻሉን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ተረፈ አራርሳ ለኢዜአ እንደገለጹት በዞኑ ባለፉት አሥር ወራት የተሻለ የማር ምርት ለማግኘት ታቅዶ ሲሰራ ቆይቷል።

ለእዚህም የማር ልማት ኢኒሼቲቭን ከመተግበር ባለፈ የአርሶ አደሮች ግንዛቤ በማሳደግ ምርታማነትና የልማቱን ተሳታፊዎች ተጠቃሚነት ለማሳደግ መቻሉን ነው የተናገሩት።

እንደ ሀላፊው ገለጻ አርሶ አደሮቹ ከባህላዊ ቀፎ ወደ ዘመናዊ ቆፎ ተሸጋግረው ውጤታማ እንዲሆኑ ግንዛቤያቸውን የማሳደግ ሥራ የተሰራ ሲሆን የንብ ቀፎ ድጋፍም ተደርጎላቸዋል።

በዚህም በቡድን ተደራጅተው በንብ ማነብ ሥራ ለተሰማሩ አርሶ አደሮችና ወጣቶች ከ46 ሺህ በላይ ዘመናዊ የንብ ቀፎዎች መከፋፈሉን የጠቆሙት አቶ ተረፈ በዚህም አበረታች ውጤት ተገኝቷል ብለዋል።

በልማቱ ከ24 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችና ወጣቶች የተሳተፉ ሲሆን በዚህም ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል።

ከልማቱ ተሳታፊ አርሶ አደሮች መካከል የወልመራ ወረዳ አርሶ አደር አቶ ጌታቸው ደንደና እንዳሉት በተሰጣቸው 5 ዘመናዊ ቀፎዎች በንብ ማነብ ሥራ ተሰማርተው ተጠቀሚ መሆን ችለዋል።


ልማቱን በማስፋፋት በዚህ ዓመት የቀፎዎቹን ቁጥር ወደ 22 ማሳደግ እንደቻሉ ተናግረዋል።

ከአንድ ባህላዊ ቀፎ እስከ 5 ኪሎ ግራም ማር ያገኙ የነበረው በአሁኑ ወቅት ከእያንዳንዱ ዘመናዊ ቀፎ 12 ኪሎ ግራም ማር ማግኘት መቻላቸውን ገልጸዋል።

ዘንድሮ ከ22 ዘመናዊና አንድ ባህላዊ ቀፎዎች 269 ኪሎ ግራም ማር በማግኘታቸው ሥራውን ይበልጥ ለማስፋፋት እንዳነሳሳቸውም ነው የተናገሩት፡፡

ሌላው በአምቦ ወረዳ ጎሱ ቆራ ቀበሌ የሚኖሩት አቶ ወልደሰማያት ለታ በበኩላቸው የንብ ማነብ ስራን የሚያከናውኑት ከመደበኛ እርሻ ሥራ ጐን ለጐን በመሆኑ ከዘርፉ ባገኙት ገቢ ኑሯቸው እየተሻሻለ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡


ካሏቸው 38 ዘመናዊ፣ የሽግግርና ባህላዊ ቀፎዎች በዓመት ሁለት ጊዜ በማምረት ለገበያ ማቅረባቸውን ገልጸው በቀጣይ በስፋት ለማምረት እየተዘጋጁ መሆናቸው አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026