
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2017 (ኢዜአ)፦ የ21ኛው ክፍለ ዘመን የዓለም የፋይናንስ መዋቅር ለሁሉም የሚሰራ መሆን አለበት ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ።
አራተኛው ዓለም አቀፍ የዘላቂ ልማት ፋይናንስ ኮንፍረንስ በስፔን ሲቪያ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
“የግሉን ዘርፍ የንግድ እና ፋይናንስ አቅሞች መጠቀም” በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ ውይይት ከኮንፍረንሱ ጎን ለጎን ተካሄዷል።
የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ የአፍሪካ ሙሉ የኢኮኖሚ አቅምን ለመጠቀም በዓለም የፋይናንስ ስርዓት ላይ አፋጣኝ ማሻሻያዎችን ማድረግ እንደሚገባ አመልክተዋል።
የግሉ ዘርፍ የንግድ እና ፋይናንስ ስራ ተደጋጋፊ ብቻ ሳይሆኑ ለሁሉን አቀፍ እድገት፣ ስራ እድል ፈጠራ እና ለአረንጓዴ ሽግግር ቁልፍ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል።

በሌላ በኩል የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ለአህጉሪቷ ትልቅ ለውጥ የፈጠረ ነው ያሉት ሊቀ መንበሩ ለአነስተኛ፣ መካከለኛ እና ከፍተኛ ኢንተርፕራይዞች የሚደረገውን ድጋፍ መጨመር፣ ዘላቂ ፋይናንስ ማበረታት እና የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት የመሳብ አቅም ማሳደግ እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል።
አፍሪካ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ወጣት ያለባት፣ በተፈጥሮ ሀብት የበለጸገች እና እየተለወጠች ያለች አህጉር ናት ብለዋል።
የካፒታል አቅምን ቅድሚያ ከሚሰጣቸው የልማት አጀንዳዎች ጋር ማስተሳሰር ወሳኝ መሆኑን የተናገሩት ሊቀ መንበሩ ለዚህም 21ኛውን ክፍለ ዘመን የሚመጥን እና ለሁሉም የሚሰራ ዘመናዊ የፋይናንስ ስርዓት መገንባት እንደሚገባ መግለጻቸውን የአፍሪካ ህብረት ለኢዜአ በላከው መረጃ አስታውቋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026