
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2017 (ኢዜአ)፦ የ21ኛው ክፍለ ዘመን የዓለም የፋይናንስ መዋቅር ለሁሉም የሚሰራ መሆን አለበት ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ።
አራተኛው ዓለም አቀፍ የዘላቂ ልማት ፋይናንስ ኮንፍረንስ በስፔን ሲቪያ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
“የግሉን ዘርፍ የንግድ እና ፋይናንስ አቅሞች መጠቀም” በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ ውይይት ከኮንፍረንሱ ጎን ለጎን ተካሄዷል።
የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ የአፍሪካ ሙሉ የኢኮኖሚ አቅምን ለመጠቀም በዓለም የፋይናንስ ስርዓት ላይ አፋጣኝ ማሻሻያዎችን ማድረግ እንደሚገባ አመልክተዋል።
የግሉ ዘርፍ የንግድ እና ፋይናንስ ስራ ተደጋጋፊ ብቻ ሳይሆኑ ለሁሉን አቀፍ እድገት፣ ስራ እድል ፈጠራ እና ለአረንጓዴ ሽግግር ቁልፍ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል።

በሌላ በኩል የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ለአህጉሪቷ ትልቅ ለውጥ የፈጠረ ነው ያሉት ሊቀ መንበሩ ለአነስተኛ፣ መካከለኛ እና ከፍተኛ ኢንተርፕራይዞች የሚደረገውን ድጋፍ መጨመር፣ ዘላቂ ፋይናንስ ማበረታት እና የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት የመሳብ አቅም ማሳደግ እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል።
አፍሪካ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ወጣት ያለባት፣ በተፈጥሮ ሀብት የበለጸገች እና እየተለወጠች ያለች አህጉር ናት ብለዋል።
የካፒታል አቅምን ቅድሚያ ከሚሰጣቸው የልማት አጀንዳዎች ጋር ማስተሳሰር ወሳኝ መሆኑን የተናገሩት ሊቀ መንበሩ ለዚህም 21ኛውን ክፍለ ዘመን የሚመጥን እና ለሁሉም የሚሰራ ዘመናዊ የፋይናንስ ስርዓት መገንባት እንደሚገባ መግለጻቸውን የአፍሪካ ህብረት ለኢዜአ በላከው መረጃ አስታውቋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026