የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የ21ኛው ክፍለ ዘመን የዓለም የፋይናንስ መዋቅር ሁሉንም ያማከለ መሆን አለበት- መሐሙድ አሊ ዩሱፍ

Jul 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2017 (ኢዜአ)፦ የ21ኛው ክፍለ ዘመን የዓለም የፋይናንስ መዋቅር ለሁሉም የሚሰራ መሆን አለበት ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ።

አራተኛው ዓለም አቀፍ የዘላቂ ልማት ፋይናንስ ኮንፍረንስ በስፔን ሲቪያ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

“የግሉን ዘርፍ የንግድ እና ፋይናንስ አቅሞች መጠቀም” በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ ውይይት ከኮንፍረንሱ ጎን ለጎን ተካሄዷል።

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ የአፍሪካ ሙሉ የኢኮኖሚ አቅምን ለመጠቀም በዓለም የፋይናንስ ስርዓት ላይ አፋጣኝ ማሻሻያዎችን ማድረግ እንደሚገባ አመልክተዋል።

የግሉ ዘርፍ የንግድ እና ፋይናንስ ስራ ተደጋጋፊ ብቻ ሳይሆኑ ለሁሉን አቀፍ እድገት፣ ስራ እድል ፈጠራ እና ለአረንጓዴ ሽግግር ቁልፍ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል።


በሌላ በኩል የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ለአህጉሪቷ ትልቅ ለውጥ የፈጠረ ነው ያሉት ሊቀ መንበሩ ለአነስተኛ፣ መካከለኛ እና ከፍተኛ ኢንተርፕራይዞች የሚደረገውን ድጋፍ መጨመር፣ ዘላቂ ፋይናንስ ማበረታት እና የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት የመሳብ አቅም ማሳደግ እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል።

አፍሪካ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ወጣት ያለባት፣ በተፈጥሮ ሀብት የበለጸገች እና እየተለወጠች ያለች አህጉር ናት ብለዋል።

የካፒታል አቅምን ቅድሚያ ከሚሰጣቸው የልማት አጀንዳዎች ጋር ማስተሳሰር ወሳኝ መሆኑን የተናገሩት ሊቀ መንበሩ ለዚህም 21ኛውን ክፍለ ዘመን የሚመጥን እና ለሁሉም የሚሰራ ዘመናዊ የፋይናንስ ስርዓት መገንባት እንደሚገባ መግለጻቸውን የአፍሪካ ህብረት ለኢዜአ በላከው መረጃ አስታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026