
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 25/2017 (ኢዜአ)፦ የ21ኛው ክፍለ ዘመን የዓለም የፋይናንስ መዋቅር ለሁሉም የሚሰራ መሆን አለበት ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ።
አራተኛው ዓለም አቀፍ የዘላቂ ልማት ፋይናንስ ኮንፍረንስ በስፔን ሲቪያ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
“የግሉን ዘርፍ የንግድ እና ፋይናንስ አቅሞች መጠቀም” በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ ውይይት ከኮንፍረንሱ ጎን ለጎን ተካሄዷል።
የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ የአፍሪካ ሙሉ የኢኮኖሚ አቅምን ለመጠቀም በዓለም የፋይናንስ ስርዓት ላይ አፋጣኝ ማሻሻያዎችን ማድረግ እንደሚገባ አመልክተዋል።
የግሉ ዘርፍ የንግድ እና ፋይናንስ ስራ ተደጋጋፊ ብቻ ሳይሆኑ ለሁሉን አቀፍ እድገት፣ ስራ እድል ፈጠራ እና ለአረንጓዴ ሽግግር ቁልፍ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል።

በሌላ በኩል የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ለአህጉሪቷ ትልቅ ለውጥ የፈጠረ ነው ያሉት ሊቀ መንበሩ ለአነስተኛ፣ መካከለኛ እና ከፍተኛ ኢንተርፕራይዞች የሚደረገውን ድጋፍ መጨመር፣ ዘላቂ ፋይናንስ ማበረታት እና የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት የመሳብ አቅም ማሳደግ እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል።
አፍሪካ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ወጣት ያለባት፣ በተፈጥሮ ሀብት የበለጸገች እና እየተለወጠች ያለች አህጉር ናት ብለዋል።
የካፒታል አቅምን ቅድሚያ ከሚሰጣቸው የልማት አጀንዳዎች ጋር ማስተሳሰር ወሳኝ መሆኑን የተናገሩት ሊቀ መንበሩ ለዚህም 21ኛውን ክፍለ ዘመን የሚመጥን እና ለሁሉም የሚሰራ ዘመናዊ የፋይናንስ ስርዓት መገንባት እንደሚገባ መግለጻቸውን የአፍሪካ ህብረት ለኢዜአ በላከው መረጃ አስታውቋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026