🔇Unmute
አዲስ አበባ፤መስከረም 29/2018(ኢዜአ)፦ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የጋራ ተጠቃሚነትን እውን ከማድረግ ባሻገር ሜጋ ፕሮጀክቶችን በራስ አቅም ሰርቶ ማጠናቀቅ እንደሚቻል ያረጋገጥንበት ነው ሲሉ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት አመራር አባላት ገለጹ።
የኢንስቲትዩት አመራር አባላት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ጎብኝተዋል።
የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጽህፈት ቤት ኃላፊ ከበደ ቶሎሳ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ታላቁ የህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያንን የብዙ ዘመን ምኞት እውን ያደረገ ፕሮጀክት ነው።
ታላቁ ህዳሴ ግድብ መላው ኢትዮጵያውያንን ወደ ብርሀን ያመጣ የድል ብስራት መሆኑን ጠቁመው፤ አገሪቷ ከድህነት የምትወጣበትን አቅጣጫ ያሳየ ታላቅ ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል።
ኢንስቲትዩቱ ለግድቡ በተለያዩ መንገዶች የቴክኖሎጂ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን ገልጸው፤ ዲጂታላይዜሽንን ለማረጋገጥ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው አመልክተዋል።
የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የሰው ሀብት ልማት እና አስተዳደር ዳይሬክተር ግርማቸው ጌቱ በበኩላቸው፤ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያ የያዘቻቸውን ስትራቴጂያዊ ግቦች የሚያሳካ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል።
እንዲሁም በራስ አቅም መልማት እና ማደግ እንደሚቻል ትምህርት የሰጠ ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል።
ታላቁ ህዳሴ ግድቡ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ትልቅ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸው፤ በቀጣይም ሌሎች ፕሮጀክቶችን በራስ አቅም ማጠናቀቅ እንደሚቻል ያስተማረ መሆኑን ተናግረዋል።
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የጋራ ተጠቃሚነትን እውን ከማድረግ ባሻገር ሜጋ ፕሮጀክቶችን በራስ አቅም ሰርቶ ማጠናቀቅ እንደሚቻል የታየበት መሆኑን ገልጸዋል።
አብዛኛው ቴክኖሎጂ የኤሌክትሪክ ሀይል እንደሚፈልግ ገልጸው፤ ቀጣይ በመንግስት የተያዙ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ከመደገፍ አኳያም ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026