የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሜጋ ፕሮጀክቶችን በራስ አቅም ሰርቶ ማጠናቀቅ እንደሚቻል ያረጋገጥንበት ነው

Oct 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤መስከረም 29/2018(ኢዜአ)፦ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የጋራ ተጠቃሚነትን እውን ከማድረግ ባሻገር ሜጋ ፕሮጀክቶችን በራስ አቅም ሰርቶ ማጠናቀቅ እንደሚቻል ያረጋገጥንበት ነው ሲሉ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት አመራር አባላት ገለጹ።

የኢንስቲትዩት አመራር አባላት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ጎብኝተዋል።

የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጽህፈት ቤት ኃላፊ ከበደ ቶሎሳ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ታላቁ የህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያንን የብዙ ዘመን ምኞት እውን ያደረገ ፕሮጀክት ነው።

ታላቁ ህዳሴ ግድብ መላው ኢትዮጵያውያንን ወደ ብርሀን ያመጣ የድል ብስራት መሆኑን ጠቁመው፤ አገሪቷ ከድህነት የምትወጣበትን አቅጣጫ ያሳየ ታላቅ ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል።

ኢንስቲትዩቱ ለግድቡ በተለያዩ መንገዶች የቴክኖሎጂ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን ገልጸው፤ ዲጂታላይዜሽንን ለማረጋገጥ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የሰው ሀብት ልማት እና አስተዳደር ዳይሬክተር ግርማቸው ጌቱ በበኩላቸው፤ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያ የያዘቻቸውን ስትራቴጂያዊ ግቦች የሚያሳካ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል።

እንዲሁም በራስ አቅም መልማት እና ማደግ እንደሚቻል ትምህርት የሰጠ ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል።

ታላቁ ህዳሴ ግድቡ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ትልቅ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸው፤ በቀጣይም ሌሎች ፕሮጀክቶችን በራስ አቅም ማጠናቀቅ እንደሚቻል ያስተማረ መሆኑን ተናግረዋል።

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የጋራ ተጠቃሚነትን እውን ከማድረግ ባሻገር ሜጋ ፕሮጀክቶችን በራስ አቅም ሰርቶ ማጠናቀቅ እንደሚቻል የታየበት መሆኑን ገልጸዋል።

አብዛኛው ቴክኖሎጂ የኤሌክትሪክ ሀይል እንደሚፈልግ ገልጸው፤ ቀጣይ በመንግስት የተያዙ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ከመደገፍ አኳያም ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026