🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፦ በግብርናው ዘርፍ የኢትዮጵያን ማንሰራራት ዕውን የሚያደርጉ ውጤታማ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ገለጹ።
የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋን ጨምሮ የዘርፉ ከፍተኛ አመራሮች በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቀቤና ልዩ ወረዳ በክላስተር የለማ የበቆሎ እርሻን ተመልክተዋል።

በምልከታው የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለሰ መኮንን(ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ማንደፍሮ ንጉሴ(ዶ/ር)፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የግብርና ቢሮ ኃላፊ ኡስማን ሱሩር እና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ በዚሁ ወቅት፤ ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ የጀመረቻቸው ስራዎች ውጤት እያስገኙ ነው ብለዋል።
በምርት ዘመኑ በተለያዩ ሰብሎች ከለማው ማሳ ውስጥ ከ12 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በክላስተር መልማቱን ጠቁመዋል።
በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ ያሉ ውጤታማ ተግባራት የኢትዮጵያን ማንሰራራት ዕውን የሚያደርጉ መሆናቸውንም ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
በቀቤና ልዩ ወረዳ በምርት ዘመኑ 12ሺህ 500 ሄክታር መሬት በበቆሎ የለማ ሲሆን በልዩ ወረዳው በዓመት አራት ጊዜ የግብርና ልማት እንደሚከናወን ተገልጿል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025