🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፦ በግብርናው ዘርፍ የኢትዮጵያን ማንሰራራት ዕውን የሚያደርጉ ውጤታማ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ገለጹ።
የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋን ጨምሮ የዘርፉ ከፍተኛ አመራሮች በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቀቤና ልዩ ወረዳ በክላስተር የለማ የበቆሎ እርሻን ተመልክተዋል።

በምልከታው የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለሰ መኮንን(ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ማንደፍሮ ንጉሴ(ዶ/ር)፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የግብርና ቢሮ ኃላፊ ኡስማን ሱሩር እና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ በዚሁ ወቅት፤ ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ የጀመረቻቸው ስራዎች ውጤት እያስገኙ ነው ብለዋል።
በምርት ዘመኑ በተለያዩ ሰብሎች ከለማው ማሳ ውስጥ ከ12 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በክላስተር መልማቱን ጠቁመዋል።
በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ ያሉ ውጤታማ ተግባራት የኢትዮጵያን ማንሰራራት ዕውን የሚያደርጉ መሆናቸውንም ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
በቀቤና ልዩ ወረዳ በምርት ዘመኑ 12ሺህ 500 ሄክታር መሬት በበቆሎ የለማ ሲሆን በልዩ ወረዳው በዓመት አራት ጊዜ የግብርና ልማት እንደሚከናወን ተገልጿል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026