የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በሲዳማ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራት ለኢንዱስትሪ ግብአት አቅም ፈጥረዋል

Oct 13, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ ፤ ጥቅምት 1/2018 (ኢዜአ)፡- በሲዳማ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራት ለኢንዱስትሪ ግብአትና ገበያን ለማረጋጋት አቅም መፍጠራቸውን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።

"ምርታማነትን ማሳደግ ለቤተሰብ ብልጽግና" በሚል መሪ ሀሳብ የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ አመታዊ የሴክተር ጉባኤ በሃዋሳ እየተካሄደ ነው።

የቢሮው ሃላፊ አቶ መምሩ ሞኬ በዚህ ጊዜ እንደገለጹት በክልሉ የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል።


በሰብል ልማት፣ በበጋ መስኖና በቡና ልማት ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ለኢንዱስትሪ ግብአት የሚሆኑና ገበያን ማረጋጋት የሚያስችል አቅም መፍጠራቸውን ገልጸዋል ።

በሂደቱም ከፍተኛ የስራ እድል መፈጠሩን የጠቀሱት ሃላፊው በ2016/17 የምርት ዘመን የመኸር ወቅት ከ106 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዋና ዋና ሰብሎች መልማቱን አስታውሰዋል።

በበልግ የለማውን 72 ሺህ ሄክታር ጨምሮ ከ319 ሺህ ኩንታል በላይ ማዳበሪያ የቀረበ ሲሆን በምርጥ ዘርና በቴክኖሎጂ አጠቃቀም ካለፉት አመታት የተሻለ አፈጻጸም መኖሩን ተናግረዋል።

የቡና ምርታማነትን ለማሳደግ ኢንዱስትሪዎችና ባለሃብቶችን በማሳተፍ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለቡና አብቃይ አካባቢዎች መድረሱን ገልጸዋል።

በዚህም የቡና ምርታማነት ማደጉን ጠቅሰው በተጠናቀቀው በጀት አመት 39 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለማእከላዊ ገበያ ማቅረብ ተችሏል ብለዋል።

በበጋ መስኖም በሚለማው መሬት ሽፋንና በምርታማነት ለውጥ የተመዘገበ ሲሆን የአትክልት ልማት ስራው ገበያን ማረጋጋት የሚያስችል አቅም የተፈጠረበት መሆኑን ገልጸዋል።

በቴክኖሎጂ፣ የውሃ አማራጮችን አሟጦ በመጠቀምና ምርታማነትን ማሳደግ ላይ የሚታዩ ውስንነቶችን ማረም ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን የቢሮው ሃላፊ አቶ መምሩ ገልጸዋል።

የሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪና የገጠር ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ ዱሬሳ ሌዳሞ በበኩላቸው በዞኑ አርሶ አደሮችን በክላስተር በማደራጀት ከ26 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ማልማት እንደተቻለ ገልጸዋል።


በዚህም ከ75 ሺህ 400 በላይ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ከማድረግ ባለፈ ከ7 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ማምረት መቻሉን ተናግረዋል።

በቴክኖሎጂ አጠቃቀም የታየው ለውጥ የዝናብ መቆራረጥ ባጋጠማቸው አካባቢዎች የምርት እጥረት እንዳያጋጥም አስችሏል ያሉት ደግሞ የማእከላዊ ሲዳማ ዞን ገጠር ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ለጠፈ ላንቻ ናቸው።


በዘንድሮው የመስኖ ልማት ስራ ከ14 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ ላይ ገበያ ተኮር ምርቶች እንደሚመረቱ ተናግረዋል።

በመድረኩ የክልሉ መንግስት ረዳት ተጠሪ አስፋው ጎኖሶን ጨምሮ የመዋቅሩ ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ሴክተሮች እውቅና ተሰጥቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025