🔇Unmute
ጎንደር፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ):-የጎንደር ከተማ አስተዳደር በስሩ ባሉ ሁለት የገጠር ቀበሌዎች የገጠር ኮሪደር ልማትን ተግባራዊ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ተናገሩ፡፡
ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው አቶ ቻላቸው ዳኘው ለኢዜአ እንደገለጹት የገጠር ኮሪደር ልማቱ የሚተገበረው በአዘዞ ተክለሃይማኖት እና ሳቢያ ሳይና በተባሉ ሁለት የገጠር ቀበሌዎች ነው።
በአሁኑ ወቅትም የኮሪደር ልማቱን የሚመሩ ኮሚቴዎችን ከማቋቋም ባለፈ ከሚተገበርባቸው ቀበሌዎች የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት በማድረግ መግባባት ላይ መደረሱን ገልጸዋል።
የኮሪደር ልማቱን ለማስተግበር የሚያስችል ዕቅድ በማዘጋጀት በተያዘው በጀት ዓመት ሥራውን ለማከናወን እየተሰራ መሆኑንም አቶ ቻላቸው ተናግረዋል፡፡
በልማቱም ሞዴል የአርሶ አደር መኖሪያ ቤቶች፣ የመንገድ፣ የንጹህ መጠጥ ውሃና በታዳሽ ሃይል ላይ የተመሰረቱ የኢነርጂ አማራጮች እንደሚተገበሩ ነው የገለጹት።
የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን የኑሮ ዘይቤ በመቀየር ዘመናዊ አኗኗርን የሚያጎናጽፍና አዲስ የአስተሳሰብ እይታን የሚያሰፋ በመሆኑ ለሀገራዊ እድገት መሰረት መሆኑን ተናግረዋል።
በጎንደር ከተማ እየተገነባ ያለው ሁለተኛው ምዕራፍ የከተማ የኮሪደር ልማት ሥራ በጥራትና በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑ ተመልክቷል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026