🔇Unmute
ጎንደር፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ):-የጎንደር ከተማ አስተዳደር በስሩ ባሉ ሁለት የገጠር ቀበሌዎች የገጠር ኮሪደር ልማትን ተግባራዊ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ተናገሩ፡፡
ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው አቶ ቻላቸው ዳኘው ለኢዜአ እንደገለጹት የገጠር ኮሪደር ልማቱ የሚተገበረው በአዘዞ ተክለሃይማኖት እና ሳቢያ ሳይና በተባሉ ሁለት የገጠር ቀበሌዎች ነው።
በአሁኑ ወቅትም የኮሪደር ልማቱን የሚመሩ ኮሚቴዎችን ከማቋቋም ባለፈ ከሚተገበርባቸው ቀበሌዎች የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት በማድረግ መግባባት ላይ መደረሱን ገልጸዋል።
የኮሪደር ልማቱን ለማስተግበር የሚያስችል ዕቅድ በማዘጋጀት በተያዘው በጀት ዓመት ሥራውን ለማከናወን እየተሰራ መሆኑንም አቶ ቻላቸው ተናግረዋል፡፡
በልማቱም ሞዴል የአርሶ አደር መኖሪያ ቤቶች፣ የመንገድ፣ የንጹህ መጠጥ ውሃና በታዳሽ ሃይል ላይ የተመሰረቱ የኢነርጂ አማራጮች እንደሚተገበሩ ነው የገለጹት።
የገጠር ኮሪደር ልማት የአርሶ አደሩን የኑሮ ዘይቤ በመቀየር ዘመናዊ አኗኗርን የሚያጎናጽፍና አዲስ የአስተሳሰብ እይታን የሚያሰፋ በመሆኑ ለሀገራዊ እድገት መሰረት መሆኑን ተናግረዋል።
በጎንደር ከተማ እየተገነባ ያለው ሁለተኛው ምዕራፍ የከተማ የኮሪደር ልማት ሥራ በጥራትና በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑ ተመልክቷል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026