የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በኢትዮጵያ ቁልፍ የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ላይ የሚቃጡ የሳይበር ጥቃቶችን ምላሽ መስጠት የሚያስችል አቅም ተገንብቷል

Oct 15, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ቁልፍ የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ላይ የሚቃጡ የሳይበር ጥቃቶችን ምላሽ መስጠት የሚያስችል አቅም መገንባቱን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሀሚድ ገለጹ፡፡

የአስተዳደሩ ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሀሚድ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ባለፉት አምስት ዓመታት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ተቀርፆ ተግባራዊ ተደረጓል።

ስትራቴጂው ዲጂታላይዜሽን፣ ዘመናዊ አገልግሎት አሰጣጥ አና ቴክኖሎጂን ማዕከል ያደረገ በመሆኑ በሁሉም መስኮች ገቢራዊ እንዲሆን በትኩረት መሰራቱን ገልጸዋል፡፡

ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ዜጎች በቴክኖሎጂ ላይ ያላቸውን አረዳድ በማሳደግ ለዲጂታል መስፋፋት ዕድል ፈጥሯል ብለዋል፡፡

ይሁን እንጂ ከቴክኖሎጂ መስፋፋት ጋር ተያይዞ የሳይበር ጥቃት ይዘቱንና አይነቱን እየቀያየረ እየተከሰተ መሆኑንም አንስተዋል፡፡

በዚህም የሳይበር ጥቃትን ቀድሞ መከላከል የሚያስችል አቅም መገንባት በሚያስችል የወትሮ ዝግጁነት የአሰራር ሥርዓት የቁጥጥርና ምላሽ መስጫ ማዕከላትን በማቋቋም ሁልጊዜም በተጠንቀቅ እየሰራን ነው ብለዋል፡፡

ማዕከላቱን በቴክኖሎጂና በብቁ የሰው ኃይል በማሟላት የቅድመ መከላከልና ዓለም አቀፍ የቁጥጥር ስርዓት በመዘርጋት ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል፡፡

አስተዳደሩ በጥናት የተደገፈ የህግ ማዕቀፍ በማዘጋጀት፣ ፖሊሲና ስትራቴጂ በመቅረጽ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የአሰራር ሥርዓት ዘርግቷል ብለዋል፡፡

ባለፈው ዓመት ዘመኑን የዋጀ አዲስ የሳይበር ደህንነት ፖሊሲ መጽደቁን ገልጸው፤ ፖሊሲው ዲጂታላይዜሽንን ከማስረጽ ባሻገር የሳይበር ጥቃትን ለመከላከል ተደራሽነትን ማስፋት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በታዳጊዎች የሰመር ካምፕ የሳይበር ታለንት ማዕከል የሚሰጠው ትምህርት፣ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር የሚሰሩ የጥናትና ምርምር ስራዎች የዜጎችን ግንዛቤ በማሳደግ ገንቢ ሚና እየተወጡ እንደሚገኙም ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025