🔇Unmute
ድሬዳዋ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ ጀግናው አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ በድሬዳዋ ኢንቨስት ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ገለጸ።
አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ ከአስተዳደሩ ከንቲባ እና ሌሎችም አመራሮች ጋር በመሆን የድሬዳዋን የኢንቨስትመንት አማራጮችና መሠረተ ልማት ስራዎች ተዘዋውሮ ተመልክቷል።

ከጉብኝቱም በኋላ ከከንቲባ ከድር ጁሃር እና ካቢኔያቸው ጋር የተወያየ ሲሆን የድሬዳዋን መሠረተ ልማት አቅርቦትና የልማት አማራጮች አድንቋል።
የነፃ ንግድ ቀጣና፣ የደረቅ ወደብ እና የኮንቬንሽን ማዕከል ኢንቨስትመንት ለመጀመር ሳቢ መሆናቸውን በማንሳት ኢንቨስት የማድረግ ፍላጎትና ዝግጁነት ያለው መሆኑን አረጋግጧል።
በከተማዋ እየተከናወነ ያለው የልማት እንቅስቃሴ ከተማዋን የኮንፈረንስ ቱሪዝም ማእከል ለማድረግ የሚያስችል እንዲሁም በሆቴልና መስተንግዶ ዘርፍ ኢንቨስት ለማድረግ አመቺ ነው ሲልም አክሏል።

ድሬዳዋን የንግድ፣ የኢንዱስትሪ እና የቱሪዝም ኮንፈረንስ ከተማ ለማድረግ በከተማው የተጀመሩ ስራዎች ኢንቨስት ለማድረግ ስለሚያመቹ ሌሎች ባለሃብቶችም በዘርፉ እንዲሰማሩ ምክረ ሀሳቡን አጋርቷል።
ከተማዋ በጎብኚዎች ተመራጭ የሚያደርጋት የአየር ንብረት እና የተፈጥሮ ጸጋን የታደለች መሆኗን ገልፆ ይህም ለሆቴል ኢንቨስትመንቱ መሳካት ተጨማሪ አቅም እንደሚሆንም አመልክቷል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026