የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በድሬዳዋ ኢንቨስት ለማድረግ ተዘጋጅቻለው-አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ

Oct 15, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ድሬዳዋ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ ጀግናው አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ በድሬዳዋ ኢንቨስት ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ገለጸ።

አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ ከአስተዳደሩ ከንቲባ እና ሌሎችም አመራሮች ጋር በመሆን የድሬዳዋን የኢንቨስትመንት አማራጮችና መሠረተ ልማት ስራዎች ተዘዋውሮ ተመልክቷል።


ከጉብኝቱም በኋላ ከከንቲባ ከድር ጁሃር እና ካቢኔያቸው ጋር የተወያየ ሲሆን የድሬዳዋን መሠረተ ልማት አቅርቦትና የልማት አማራጮች አድንቋል።

የነፃ ንግድ ቀጣና፣ የደረቅ ወደብ እና የኮንቬንሽን ማዕከል ኢንቨስትመንት ለመጀመር ሳቢ መሆናቸውን በማንሳት ኢንቨስት የማድረግ ፍላጎትና ዝግጁነት ያለው መሆኑን አረጋግጧል።

በከተማዋ እየተከናወነ ያለው የልማት እንቅስቃሴ ከተማዋን የኮንፈረንስ ቱሪዝም ማእከል ለማድረግ የሚያስችል እንዲሁም በሆቴልና መስተንግዶ ዘርፍ ኢንቨስት ለማድረግ አመቺ ነው ሲልም አክሏል።


ድሬዳዋን የንግድ፣ የኢንዱስትሪ እና የቱሪዝም ኮንፈረንስ ከተማ ለማድረግ በከተማው የተጀመሩ ስራዎች ኢንቨስት ለማድረግ ስለሚያመቹ ሌሎች ባለሃብቶችም በዘርፉ እንዲሰማሩ ምክረ ሀሳቡን አጋርቷል።

ከተማዋ በጎብኚዎች ተመራጭ የሚያደርጋት የአየር ንብረት እና የተፈጥሮ ጸጋን የታደለች መሆኗን ገልፆ ይህም ለሆቴል ኢንቨስትመንቱ መሳካት ተጨማሪ አቅም እንደሚሆንም አመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026