የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በአፋር ክልል የጤና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚያግዝ የዲጂታል አገልግሎት ተዘርግቷል

Oct 17, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሰመራ፤ ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ)፦ በአፋር ክልል የጤና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚያግዝ የዲጂታል አገልግሎት መዘርጋቱን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ።

በክልሉ የጭፍራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የዲጂታላይዝ አገልግሎት ዛሬ ወደ ስራ ገብቷል።

በአገልግሎቱ ማስጀመሪያ ስነ ስርአት ላይ የተገኙት የአፋር ክልል ጤና ቢሮ ኀላፊ አቶ ያሲን ሃቢብ እንደተናገሩት በክልሉ የጤና አገልግሎትን ጥራትና ተደራሽነት በማረጋገጥ የተገልጋዩን እርካታ ለማሳደግ እየተሰራ ነው።

የጤና አገልግሎቱን ጥራትና ተደራሽነት ለማረጋገጥ የዲጂታል መረጃ አያያዝንና የሰው ሀይል አቅም ግንባታ ላይ መሰራቱን አክለዋል።

ይህም የጤናውን ዘርፍ በተጠናከረ መረጃ በመደገፍ ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን አገልግሎት አስተማማኝና ፈጣን ለማድረግ እንደሚያስችል ተናግረዋል።

ዛሬ በይፋ ስራ የጀመረው የጭፍራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የዲጂታላይዜሽን አገልግሎትም የዚሁ ጥረት አካል ነው ብለዋል።

ከወረቀት ንክኪ ነጻ የሆነው ይህ አገልግሎት የተደራጀ የጤና መረጃን በቀላሉ ለህክምና ተግባሩ ለማዋል እንደሚያግዝ ተናግረዋል።

አገልግሎቱን በቀጣይም ወደ ሌሎች ሆስፒታሎችና ጤና ጣቢያዎች የማስቀጠል ተግባር እንደሚከናወን አመላክተዋል።

የጭፍራ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አሊ አርባ በበኩላቸው በቴክኖሎጂ የተደገፈው የሆስፒታሉ አገልግሎት መረጃን በአግባቡ በማደራጀት ግልጽነትን ከመፍጠር ባለፈ ወረፋን የሚያስቀር መሆኑን ተናግረዋል።

የጭፍራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ መሐመድ አሚን ኡመር እንዳሉት በይፋ የተጀመረው አገልግሎት ለህክምና አሰጣጥ መቀላጠፍ፣ ለጥናትና ምርምር የተደራጁ መረጃዎችን ለማግኘት እንደ መረጃ ቋት ሆኖ ያገለግላል።

በተለይም የህክምና አገልግሎትን ለማቀላጠፍ መረጃን በቀላሉ ለህክምናው ባለሞያ ተደራሽ በማድረግ ታካሚው ተገቢውን አገልግሎት እንዲያገኝ የሚያስችል ነው ብለዋል።

በጤናው ዘርፍ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ጥራት ያለውና አስተማማኝ አገልግሎት ለመስጠት ተጨማሪ እቅም እንደሚሆን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025