የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በአፋር ክልል የጤና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚያግዝ የዲጂታል አገልግሎት ተዘርግቷል

Oct 17, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሰመራ፤ ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ)፦ በአፋር ክልል የጤና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚያግዝ የዲጂታል አገልግሎት መዘርጋቱን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ።

በክልሉ የጭፍራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የዲጂታላይዝ አገልግሎት ዛሬ ወደ ስራ ገብቷል።

በአገልግሎቱ ማስጀመሪያ ስነ ስርአት ላይ የተገኙት የአፋር ክልል ጤና ቢሮ ኀላፊ አቶ ያሲን ሃቢብ እንደተናገሩት በክልሉ የጤና አገልግሎትን ጥራትና ተደራሽነት በማረጋገጥ የተገልጋዩን እርካታ ለማሳደግ እየተሰራ ነው።

የጤና አገልግሎቱን ጥራትና ተደራሽነት ለማረጋገጥ የዲጂታል መረጃ አያያዝንና የሰው ሀይል አቅም ግንባታ ላይ መሰራቱን አክለዋል።

ይህም የጤናውን ዘርፍ በተጠናከረ መረጃ በመደገፍ ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን አገልግሎት አስተማማኝና ፈጣን ለማድረግ እንደሚያስችል ተናግረዋል።

ዛሬ በይፋ ስራ የጀመረው የጭፍራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የዲጂታላይዜሽን አገልግሎትም የዚሁ ጥረት አካል ነው ብለዋል።

ከወረቀት ንክኪ ነጻ የሆነው ይህ አገልግሎት የተደራጀ የጤና መረጃን በቀላሉ ለህክምና ተግባሩ ለማዋል እንደሚያግዝ ተናግረዋል።

አገልግሎቱን በቀጣይም ወደ ሌሎች ሆስፒታሎችና ጤና ጣቢያዎች የማስቀጠል ተግባር እንደሚከናወን አመላክተዋል።

የጭፍራ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አሊ አርባ በበኩላቸው በቴክኖሎጂ የተደገፈው የሆስፒታሉ አገልግሎት መረጃን በአግባቡ በማደራጀት ግልጽነትን ከመፍጠር ባለፈ ወረፋን የሚያስቀር መሆኑን ተናግረዋል።

የጭፍራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ መሐመድ አሚን ኡመር እንዳሉት በይፋ የተጀመረው አገልግሎት ለህክምና አሰጣጥ መቀላጠፍ፣ ለጥናትና ምርምር የተደራጁ መረጃዎችን ለማግኘት እንደ መረጃ ቋት ሆኖ ያገለግላል።

በተለይም የህክምና አገልግሎትን ለማቀላጠፍ መረጃን በቀላሉ ለህክምናው ባለሞያ ተደራሽ በማድረግ ታካሚው ተገቢውን አገልግሎት እንዲያገኝ የሚያስችል ነው ብለዋል።

በጤናው ዘርፍ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ጥራት ያለውና አስተማማኝ አገልግሎት ለመስጠት ተጨማሪ እቅም እንደሚሆን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026