የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በአማራ ክልል በሩብ ዓመቱ ከሁለት ነጥብ ስምንት ሚሊዮን በላይ የአንድ ቀን ጫጬቶች ተሰራጭተዋል

Oct 23, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በሩብ ዓመቱ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ከሁለት ነጥብ ስምንት ሚሊዮን በላይ የአንድ ቀን ጫጬቶች መሰራጨታቸውን የክልሉ እንስሳትና አሣ ሃብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።

በቢሮው የዘርፉ ባለሙያ ሙላት ዳኛው ለኢዜአ እንደገለጹት የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብርን ውጤታማ ለማድረግ ለዶሮ እርባታ ተደራሽነት ትኩረት ተሰጥቷል።

ለዚህም በበጀት ዓመቱ ከ13 ሚሊዮን በላይ የአንድ ቀን ጫጩቶችን ለአርቢዎች ለማሰራጨት ታቅዶ በሩብ ዓመቱ ብቻ 2 ሚሊዮን 852ሺህ ጫጩቶችን ማሰራጨት ተችሏል ብለዋል።

‎በዕቅድ የተያዘውን ግብ ለማሳካት የዶሮ ጫጩቶችን የማስፈልፈል፣ የማሳደግና ለአርቢዎች የማሰራጨት ሥራ በቅንጅት እንደሚሰራም አክለዋል።


በዶሮ እርባታው ዘርፍ ከተሰማሩ አንቀሳቃሾቸ መካከል የዘምባባ ዶሮ እርባታ ማህበር ሊቀመንበር ወጣት ዮሴፍ ፈቃዱ እንደገለጸው፣ ማህበሩ ሰባት አባላት እንዳሉትና ከመንግስት በተሰጣቸው መስርያ ቦታ 6ሺህ የአንድ ቀን ጫጩቶችን ተረክበው በማሳደግ ላይ ናቸው።

በአሁኑ ወቅት 45 ቀን የሞላቸውን እንቁላል ጣይ ቄብ ዶሮዎችን ለአርቢዎች ለማሰራጨት በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ጠቅሷል።

በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የአንድ ቀን ጫጩቶችን አሳድጎ ለአርቢዎች ማሰራጨት ውጤታማ እንደሚያደርግ የገለፀው ደግሞ በባህር ዳር ከተማ በዘርፉ የተሰማራው ወጣት ማስተዋል አያልነህ ነው።

ሁለት ሆነው በመደራጀት በዚህ ሥራ መሰማራታቸውን ጠቁሞ በዓመት እስከ 75ሺህ ጫጩቶችን አሳድገው ለአርቢዎች በማሰራጨት ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ መሆናቸውን ተናግሯል።

ያለባቸውን የቦታ ችግር የከተማ አስተዳደሩ በቀጣይ ከፈታላቸው ተጨማሪ ጫጩቶችን ተረክበው በማሳደግ ለአርቢዎች በማሰራጨት የተሻለ ተጠቃሚ ለመሆን እንደሚሰሩም ገልጿል።

በክልሉ ባለፈው ዓመት ስድስት ነጥብ ስምንት ሚሊዮን የአንድ ቀን ጫጩቶችን በማስፈልፈል ማሰራጨታቸውን ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026