የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በአማራ ክልል በሩብ ዓመቱ ከሁለት ነጥብ ስምንት ሚሊዮን በላይ የአንድ ቀን ጫጬቶች ተሰራጭተዋል

Oct 23, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በሩብ ዓመቱ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ከሁለት ነጥብ ስምንት ሚሊዮን በላይ የአንድ ቀን ጫጬቶች መሰራጨታቸውን የክልሉ እንስሳትና አሣ ሃብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።

በቢሮው የዘርፉ ባለሙያ ሙላት ዳኛው ለኢዜአ እንደገለጹት የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብርን ውጤታማ ለማድረግ ለዶሮ እርባታ ተደራሽነት ትኩረት ተሰጥቷል።

ለዚህም በበጀት ዓመቱ ከ13 ሚሊዮን በላይ የአንድ ቀን ጫጩቶችን ለአርቢዎች ለማሰራጨት ታቅዶ በሩብ ዓመቱ ብቻ 2 ሚሊዮን 852ሺህ ጫጩቶችን ማሰራጨት ተችሏል ብለዋል።

‎በዕቅድ የተያዘውን ግብ ለማሳካት የዶሮ ጫጩቶችን የማስፈልፈል፣ የማሳደግና ለአርቢዎች የማሰራጨት ሥራ በቅንጅት እንደሚሰራም አክለዋል።


በዶሮ እርባታው ዘርፍ ከተሰማሩ አንቀሳቃሾቸ መካከል የዘምባባ ዶሮ እርባታ ማህበር ሊቀመንበር ወጣት ዮሴፍ ፈቃዱ እንደገለጸው፣ ማህበሩ ሰባት አባላት እንዳሉትና ከመንግስት በተሰጣቸው መስርያ ቦታ 6ሺህ የአንድ ቀን ጫጩቶችን ተረክበው በማሳደግ ላይ ናቸው።

በአሁኑ ወቅት 45 ቀን የሞላቸውን እንቁላል ጣይ ቄብ ዶሮዎችን ለአርቢዎች ለማሰራጨት በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ጠቅሷል።

በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የአንድ ቀን ጫጩቶችን አሳድጎ ለአርቢዎች ማሰራጨት ውጤታማ እንደሚያደርግ የገለፀው ደግሞ በባህር ዳር ከተማ በዘርፉ የተሰማራው ወጣት ማስተዋል አያልነህ ነው።

ሁለት ሆነው በመደራጀት በዚህ ሥራ መሰማራታቸውን ጠቁሞ በዓመት እስከ 75ሺህ ጫጩቶችን አሳድገው ለአርቢዎች በማሰራጨት ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ መሆናቸውን ተናግሯል።

ያለባቸውን የቦታ ችግር የከተማ አስተዳደሩ በቀጣይ ከፈታላቸው ተጨማሪ ጫጩቶችን ተረክበው በማሳደግ ለአርቢዎች በማሰራጨት የተሻለ ተጠቃሚ ለመሆን እንደሚሰሩም ገልጿል።

በክልሉ ባለፈው ዓመት ስድስት ነጥብ ስምንት ሚሊዮን የአንድ ቀን ጫጩቶችን በማስፈልፈል ማሰራጨታቸውን ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026