የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዘላቂ የኃይል አቅርቦትን በማረጋገጥ ዲጂታላይዜሽንን ለማፋጠን የሚያስችል ነው

Oct 27, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ጥቅምት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዘላቂ የኃይል አቅርቦትን በማረጋገጥ ለዲጂታላይዜሽን መፋጠን አስተዋፅኦው የጎላ መሆኑን ምሁራን ገለፁ።

ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም የተመረቀው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያ ተጨማሪ አምስት ሺህ ሜጋ ዋት በላይ ኃይል እንድታገኝ አድርጓል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 100 ቀናት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈጻጸም ግምገማን አስመልክቶ በኮይሻ ግድብ ከሚኒስትሮች ጋር ውይይት አድርገዋል።

በዚህ ወቅትም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በሚቀጥሉት ወራት ለኢነርጂ እና መስኖ አገልግሎት የሚውሉ መካከለኛ እና ከፍተኛ ግድቦች እንደሚመረቁ ገልጸዋል።

ኢዜአ ያነጋገራቸው ምሁራን እንደገለፁት፤ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተጠናቆ ወደ ሃይል አቅርቦት መግባቱ ዘላቂ የኤሌትሪክ ኃይል አቅርቦትን በማረጋገጥ ለዲጂታላይዜሽን መፋጠን አስተዋፅኦው የጎላ ነው።

በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደር ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንትና የስትራክቸራል ምህንድስና ምሁር ተመስገን ወንድሙ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የኤሌትሪክ ኃይል አቅርቦት ለዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባታ ወሳኝ ሚና አለው።

ዘላቂ የኤሊትሪክ ኃይል አቅርቦት ለዲጂታላይዜሽን መፋጠን አስተዋፅኦው የጎላ መሆኑን አንስተው፤ የታላቁ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅም ንፁህና ዘላቂ የኃይል ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።

ከታላቁ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ባለፈ እንደ ኮይሻ ያሉ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫዎች እየተጠናቀቁ መሆን የዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ አስቻይ መሆኑን ጠቁመዋል።


በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንትና የኤሌክትሪካል ፓወር ምህንድስና ምሁር ከማል ኢብራሂም (ዶ/ር)፤ የታላቁ ህዳሴ ግድብ መመረቅ የሀገሪቷን የኤሌትሪክ ኃይል አቅርቦት በእጥፍ ያሳደገ መሆኑን ተናግረዋል።

ይህም የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ዘላቂነትን በማረጋገጥ ለዲጂታል ቴክኖሎጂ መስፋፋት አስተዋፅኦ ያለው መሆኑንም ገልፀዋል።

የኤሌትሪክ ኃይል አቅርቦት ተደራሽነት መረጋገጥ ከተሜነትን በማስፋፋት ወደ ከተሞች የሚደረግን ፍልሰት ለመቀነስ የሚያግዝ መሆኑንም አስረድተዋል።

ዩኒቨርሲቲው በሰው ኃይል ልማትና በጥናትና ምርምር ዲጂታላይዜሽንን ለማፋጠን ከተለያዩ ተቋማት ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑንም አረጋግጠዋል።

የኢሌትሪክ ሃይል አቅርቦት ለድጂታላይዜሽን መስፋፋት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው ሲሆን፤ ከሃይል አቅርቦት ውጭ የዲጂታል ሥርዓት፣ ኔትወርክ፣ ዘላቂነትና ፈጠራእንደማይኖሩ ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025