የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በዲጂታል ዘርፉ ላይ የተደረገው ሪፎርም በዘርፉ ከፍተኛ  እድገት እንዲመዘገብ አድርጓል- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

Oct 29, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦በዲጂታል ዘርፉ ላይ የተደረገው ሪፎርም በዘርፉ ከፍተኛ እድገት እንዲመዘገብ ማድረጉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተካሄዷል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ለሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ ከምክር ቤቱ አባላት በቀረቡ ጥያቄዎች ላይ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ኢትዮጵያ የ2025 የዲጂታል ቴክኖሎጂ አካታች የ2030 ስትራቴጂ በመጀመር በዘርፉ የተሻለ እድገት ለማስመዝገብ እየሰራች ነው ብለዋል።

በኢትዮጵያ ኮደርስ ስልጠና 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ወጣቶች ስልጠናውን በነጻ መውሰዳቸውን ገልጸዋል።

ለውጡ በተጀመረበት ወቅት 37 ሚሊዮን የቴሌኮም ተጠቃሚዎች እንደነበሩ ገልጸው፤ በአሁኑ ወቅት ቁጥሩ 93 ሚሊዮን ደርሷል ነው ያሉት።

ይህም ሪፎርም በዘርፉ ትልቅ እድገትና ለውጥ እንዲመዘገብ ማድረጉን አመላካች ነው ብለዋል።

በአሁኑ ወቅት 55 ሚሊዮን የሚደርሱ ዜጎች ዲጂታል ባንኪንግ ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመው፤ በ2028 ዘርፉ 11 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ሃብት ያመጣል ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልፀዋል።

ከዚሁ ዘርፍ 1 ሚሊዮን ለሚደርሱ ዜጎች የስራ እድል እንደሚፈጠር የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከዚህም 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ገቢ እንደሚገኝ መተንበዩንም ነው የተናገሩት፡፡

በተለይ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፍም ሰፋፊ ለውጥና ብቃት እየተመዘገበ መሆኑን አብራርተው፤ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ጨምሮ ከሚጠበቀው በላይ ስኬታማ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በዲጂታል ዘርፉ ላይ የተካሔደው ሪፎርም ኢትዮጵያ በራሷ አቅም የዲጂታል ገበያ ላይም ስኬታማ ስራዎች እየሰራች መሆኑን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026