🔇Unmute
ጋምቤላ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በግብርና ኢንቨስትመንት ዘርፍ በተሰማሩ ባለሃብቶች ከ70 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በቅባት ሰብሎች መልማቱን የክልሉ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ።
በክልሉ በተያዘው በጀት ዓመት 1ኛ ሩብ ዓመት 2 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ካፒታል ያስመዘገቡ 55 ባለሃብቶች በተለያዩ የኢንቨስትመንት አማራጮች ለመሰማራት ፈቃድ መውሰዳቸውንም ኮሚሽኑ ገልጿል።
የክልሉ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሎው ኡቡፕ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት የክልሉን የኢንቨስትመንት እድሎችና አማራጮች በማስተዋወቅ የዘርፉን ውጤታማነት ለማጠናከር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
እየተከናወኑ ባሉት ስራዎችም ግብርናን ጨምሮ በተለያዩ የኢንቨስትመንት አማራጮች በርካታ ባለሃብቶች ወደ ክልሉ ገብተው እያለሙ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በተለይም በግብርናው ዘርፍ እየተደረገ ባለው የድጋፍና ክትትል ስራ ከ300 በላይ ባለሃብቶች በሙሉ አቅማቸው ወደ ልማት መግባታቸውን ገልጸዋል።
አልሚዎቹ በዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ70ሺህ ሄክታር በላይ መሬት የሰሊጥና የማሾ ሰብሎች ማልማታቸውን ተናግረዋል።
ተግባሩን በማጠናከር በበጀት ዓመቱ በክልሉ የተፈጠረውን አስተማማኝ ሰላምና ምቹ የኢንቨስትመንት አማራጭ በመጠቀም ከ360 የሚበልጡ ባለሃብቶችን በግብርና፣ በማዕድን፣ በኢንዲስትሪና በአገልግሎት ዘርፍ ለመቀበል ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን አስታውቀዋል።
በበጀት ዓመቱ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት በክልሉ በተጠቀሱት ዘርፎች 2 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ካፒታል ያስመዘገቡ 55 ባለሃብቶች አዲስ የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን ኮሚሽነሩ ገልጸዋል።
በግብርና ኢንቨስትመንት ከተሰማሩት ባለሃብቶች መካከል የፍቅርማሪያም አንዳርጌ እርሻ ልማት ስራ አስኪያጅ ፈንታሁን አራጋው በሰጡት አስተያየት በዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ560 ሄክታር በላይ መሬት በማሾ ሰብል ማልታቸውን ተናግረዋል።
ከለማው መሬትም ከ5ሺህ 600 ኩንታል በላይ የማሾ ምርት እንደሚጠበቅ ጠቁመው ምርቱ ካለፈው ዓመት ጀምሮ የገበያ ተፈላጊነቱ እየጨመረ መምጣቱንም አክለዋል።
ክልሉ ለእርሻ ስራ ምቹ ስነ-ምህዳርና የተራዘመ የዝናብ ስርጭት ያለው በመሆኑ በአንድ ዓመት ሁለት ጊዜ የማልማት እድል ያለ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የዚሁ እርሻ ልማት ወኪል ካሳ አስረሴ ናቸው።
በተለይም ካለፈው ዓመት ጀምሮ የማሾ፣ የሰሊጥና የሱፍ ምርት በሀገር ውስጥም ሆነ በውጪ ገቢያ ተፈላጊነቱ እየጨመረ በመምጣቱ ሌሎች ባለሃብቶችም ሰብሉን በስፋት እያለሙ መሆኑን ገልጸዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026