የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በጋምቤላ ክልል በግብርና ኢንቨስትመንት ዘርፍ በተሰማሩ ባለሃብቶች ከ70 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በቅባት ሰብሎች እየለማ ነው

Oct 31, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ጋምቤላ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በግብርና ኢንቨስትመንት ዘርፍ በተሰማሩ ባለሃብቶች ከ70 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በቅባት ሰብሎች መልማቱን የክልሉ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ።

በክልሉ በተያዘው በጀት ዓመት 1ኛ ሩብ ዓመት 2 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ካፒታል ያስመዘገቡ 55 ባለሃብቶች በተለያዩ የኢንቨስትመንት አማራጮች ለመሰማራት ፈቃድ መውሰዳቸውንም ኮሚሽኑ ገልጿል።

የክልሉ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሎው ኡቡፕ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት የክልሉን የኢንቨስትመንት እድሎችና አማራጮች በማስተዋወቅ የዘርፉን ውጤታማነት ለማጠናከር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

እየተከናወኑ ባሉት ስራዎችም ግብርናን ጨምሮ በተለያዩ የኢንቨስትመንት አማራጮች በርካታ ባለሃብቶች ወደ ክልሉ ገብተው እያለሙ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በተለይም በግብርናው ዘርፍ እየተደረገ ባለው የድጋፍና ክትትል ስራ ከ300 በላይ ባለሃብቶች በሙሉ አቅማቸው ወደ ልማት መግባታቸውን ገልጸዋል።

አልሚዎቹ በዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ70ሺህ ሄክታር በላይ መሬት የሰሊጥና የማሾ ሰብሎች ማልማታቸውን ተናግረዋል።

ተግባሩን በማጠናከር በበጀት ዓመቱ በክልሉ የተፈጠረውን አስተማማኝ ሰላምና ምቹ የኢንቨስትመንት አማራጭ በመጠቀም ከ360 የሚበልጡ ባለሃብቶችን በግብርና፣ በማዕድን፣ በኢንዲስትሪና በአገልግሎት ዘርፍ ለመቀበል ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን አስታውቀዋል።

በበጀት ዓመቱ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት በክልሉ በተጠቀሱት ዘርፎች 2 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ካፒታል ያስመዘገቡ 55 ባለሃብቶች አዲስ የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን ኮሚሽነሩ ገልጸዋል።

በግብርና ኢንቨስትመንት ከተሰማሩት ባለሃብቶች መካከል የፍቅርማሪያም አንዳርጌ እርሻ ልማት ስራ አስኪያጅ ፈንታሁን አራጋው በሰጡት አስተያየት በዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ560 ሄክታር በላይ መሬት በማሾ ሰብል ማልታቸውን ተናግረዋል።

ከለማው መሬትም ከ5ሺህ 600 ኩንታል በላይ የማሾ ምርት እንደሚጠበቅ ጠቁመው ምርቱ ካለፈው ዓመት ጀምሮ የገበያ ተፈላጊነቱ እየጨመረ መምጣቱንም አክለዋል።

ክልሉ ለእርሻ ስራ ምቹ ስነ-ምህዳርና የተራዘመ የዝናብ ስርጭት ያለው በመሆኑ በአንድ ዓመት ሁለት ጊዜ የማልማት እድል ያለ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የዚሁ እርሻ ልማት ወኪል ካሳ አስረሴ ናቸው።

በተለይም ካለፈው ዓመት ጀምሮ የማሾ፣ የሰሊጥና የሱፍ ምርት በሀገር ውስጥም ሆነ በውጪ ገቢያ ተፈላጊነቱ እየጨመረ በመምጣቱ ሌሎች ባለሃብቶችም ሰብሉን በስፋት እያለሙ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026