የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ከንጋት ሃይቅ የሚገኘውን የዓሳ ሃብት በአግባቡ ጥቅም ላይ ማዋል የሚያስችል መመሪያ ተዘጋጅቷል

Oct 31, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡-ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ንጋት ሃይቅ የሚገኘውን የዓሳ ሃብት በአግባቡ ጥቅም ላይ ማዋል የሚያስችል መመሪያ መዘጋጀቱን የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ፍቅሩ ረጋሳ ገለጹ።

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በኢትዮጵያዊያን እውቀት፣ ጉልበትና ጥሪት ተገንብቶ ለስኬት የበቃ ታላቅ ፕሮጀክት ነው።

የህዳሴ ግድብ ግንባታ እውን መሆን ለኢትዮጵያ እድገትና ማንሰራራት አዲስ የታሪክ ምእራፍ የከፈተ የሀገር ሃብት መሆኑም ይታወቃል።

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ትሩፋት የሆነው ንጋት ሃይቅ ለዓሳ ምርትና ምርታማነት መጨመርና ለአካባቢው ተጨማሪ የኢኮኖሚ አቅም እየሆነ መጥቷል።

የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ፍቅሩ ረጋሳ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በታላቁ ህዳሴ ግድብ ላይ የተንጣለለውና ንጋት ሃይቅ በሚል የተሰየመው የውሃ ሃብት ከሌሎች ወንዞች ጋር ያለው ተፈጥሯዊ ግንኙነት ላቅ ያለ ነው።


በዚህም ሃይቁ በርካታ ተፈጥሯዊ ንጥረ ነገር በውስጡ የያዘ መሆኑ ለዓሳ ሃብት ልማት ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል ብለዋል።

በአሁኑ ወቅት ንጋት ሐይቅ 15 ሺህ ቶን ዓሳ የማምረት አቅም እንዳለው የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ይህም ለአካባቢው ማህበረሰብ ትልቅ የስራ እድል ይዞ መምጣት መቻሉን አብራርተዋል።

ከንጋት ሃይቅ የሚገኘውን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ በዘላቂነት ለማረጋገጥ ግብርና ሚኒስቴር ጥናት ማካሔዱን ገልጸዋል።

በዚህም ሀይቁን ከተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ችግሮች መከላከል አንዱና ዋነኛው መሆኑን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው፤ የሀይቁን የደህንነት ስጋት ተጋላጭነት ቀድሞ መከላከል የሚያስችል መመሪያ መዘጋጀቱን አብራርተዋል።

መመሪያው ዓሳ ማስገር የሚከናወንበትን፣ የዝርያ ማሻሻያ ስራዎችና የዓሳ መረብ አጠቃቀምን ማሻሻል የሚያስችል አሰራር የተካተተበት ስለመሆኑ አስረድተዋል።

በተጨማሪም የገበያ ትስስር በመፍጠር ከንጋት ሃይቅ የሚገኘውን የዓሳ ሃብት በአግባቡ ለገበያ ማቅረብ እንዲቻል የሚያግዝ አሰራርም እንዲሁ በመመሪያው ለማካተት ጥረት መደረጉን አብራርተዋል።


በዓሳ ምርትና ምርታማነት ዙሪያ ከሚሰሩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር ያለውን ቅንጅታዊ አሰራር ማጠናከር ላይም ትኩረት መደረጉን ጠቁመዋል።

በተለይም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና የምርምር ማዕከላት በመመሪያው አተገባበር ዙሪያ በጥናት የተደገፈ ግብዓት እንዲያቀርቡ በማድረግ በጥናት ላይ የተመሰረተ አቅጣጫ ተቀምጧል ነው ያሉት።

በአሁኑ ወቅት ንጋት ሃይቅን ተከትሎ በዓሳ ማስገር ስራ ላይ የተሰማሩ 78 ማህበራት የተደራጁ ሲሆን 35ቱ በሙሉ አቅማቸው እየሰሩ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ።

በአጠቃላይ 866 በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች የማህበራቱ አባል በመሆን የስራ እድል ተጠቃሚ መሆን ችለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026