የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ማዕከሉ ለአርሶ አደሩ አዳዲስ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማስተዋወቅ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየሰራ ነው

Nov 10, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ ጥቅምት 30/2018(ኢዜአ)፦ የአሶሳ ግብርና ምርምር ማዕከል ለአርሶ አደሩ አዳዲስ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማስተዋወቅ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ።

የምርምር ማዕከሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባምባሲ ወረዳ በምርምር ያወጣውን "BH520"(ናዳ) የተሰኘ የበቆሎ ዝርያ የመስክ ምልከታ አካሂዷል።


የምርምር ማዕከሉ ዋና ዳይሬክተር ደስታ በቀለ በወቅቱ እንደተናገሩት፤ ማዕከሉ የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በተለያዩ የሰብል አይነቶች ላይ ውጤታማ የምርምር ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል።

በማሽላ፣ በቆሎ፣ አኩሪ አተር እና ሌሎች ሰብሎች ያወጣቸው አዳዲስ ዝርያዎችን ለአርሶ አደሩ በማድረስ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ኃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑንም ገልጸዋል።


በባምባሲ ወረዳ አራት ሄክታር ማሳ ላይ እየለማ የሚገኘው "BH520"(ናዳ) የበቆሎ ዝርያ በሄክታር እስከ 95 ኩንታል ምርት የሚሰጥና አረምና ተባይን የመቋቋም አቅም ያለው ነው ብለዋል።

በተጨማሪም አዲስ የተለቀቀው የበቆሎ ዝርያ ድርቅን መቋቋም የሚችል፣ በአጭር ጊዜ የሚደርስና ምርታማነቱ የተረጋገጠ የምርምር ውጤት እንደሆነ ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል።


የባምባሲ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አብዱልዋሂድ አዙቤር በበኩላቸው፤ የምርምር ማዕከሉ በየጊዜው የሚያወጣቸው አዳዲስ ዝርያዎች አርሶ አደሩ የምግብ ዋስትናውን እንዲያረጋግጥ ከማድረግ በተጨማሪ የኢኮኖሚ አቅማቸውን እንዲያሳድጉ ትልቅ ዕገዛ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል።

አርሶ አደሩ ማዕከሉ የሚያወጣቸውን አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች በመተግበር ውጤታማ የግብርና ስራ ማከናወን እንዳለበትም አስገንዝበዋል።

በወረዳው መንደር 48 ቀበሌ እየለማ የሚገኘው አዲሱ የበቆሎ ዝርያ የሁሉንም አርሶ አደሮች ትኩረት የሳበ እና በግብርና ስራ ላይ የአርሶ አደሩን ተነሳሽነት የጨመረ ነው ያሉት ደግሞ የባምባሲ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ ጃፈር አኑር ናቸው።

በመስክ ምልክታው የክልል፣ የዞና እና የወረዳ የዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም የአካባቢው አርሶ አደሮች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025