የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ማዕከሉ ለአርሶ አደሩ አዳዲስ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማስተዋወቅ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየሰራ ነው

Nov 10, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ ጥቅምት 30/2018(ኢዜአ)፦ የአሶሳ ግብርና ምርምር ማዕከል ለአርሶ አደሩ አዳዲስ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማስተዋወቅ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ።

የምርምር ማዕከሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባምባሲ ወረዳ በምርምር ያወጣውን "BH520"(ናዳ) የተሰኘ የበቆሎ ዝርያ የመስክ ምልከታ አካሂዷል።


የምርምር ማዕከሉ ዋና ዳይሬክተር ደስታ በቀለ በወቅቱ እንደተናገሩት፤ ማዕከሉ የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በተለያዩ የሰብል አይነቶች ላይ ውጤታማ የምርምር ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል።

በማሽላ፣ በቆሎ፣ አኩሪ አተር እና ሌሎች ሰብሎች ያወጣቸው አዳዲስ ዝርያዎችን ለአርሶ አደሩ በማድረስ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ኃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑንም ገልጸዋል።


በባምባሲ ወረዳ አራት ሄክታር ማሳ ላይ እየለማ የሚገኘው "BH520"(ናዳ) የበቆሎ ዝርያ በሄክታር እስከ 95 ኩንታል ምርት የሚሰጥና አረምና ተባይን የመቋቋም አቅም ያለው ነው ብለዋል።

በተጨማሪም አዲስ የተለቀቀው የበቆሎ ዝርያ ድርቅን መቋቋም የሚችል፣ በአጭር ጊዜ የሚደርስና ምርታማነቱ የተረጋገጠ የምርምር ውጤት እንደሆነ ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል።


የባምባሲ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አብዱልዋሂድ አዙቤር በበኩላቸው፤ የምርምር ማዕከሉ በየጊዜው የሚያወጣቸው አዳዲስ ዝርያዎች አርሶ አደሩ የምግብ ዋስትናውን እንዲያረጋግጥ ከማድረግ በተጨማሪ የኢኮኖሚ አቅማቸውን እንዲያሳድጉ ትልቅ ዕገዛ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል።

አርሶ አደሩ ማዕከሉ የሚያወጣቸውን አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች በመተግበር ውጤታማ የግብርና ስራ ማከናወን እንዳለበትም አስገንዝበዋል።

በወረዳው መንደር 48 ቀበሌ እየለማ የሚገኘው አዲሱ የበቆሎ ዝርያ የሁሉንም አርሶ አደሮች ትኩረት የሳበ እና በግብርና ስራ ላይ የአርሶ አደሩን ተነሳሽነት የጨመረ ነው ያሉት ደግሞ የባምባሲ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ ጃፈር አኑር ናቸው።

በመስክ ምልክታው የክልል፣ የዞና እና የወረዳ የዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም የአካባቢው አርሶ አደሮች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026