የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በምዕራብ ጎንደር ዞን በበጋ መስኖ ከሚለማው መሬት ከ700 ሺህ ኩንታል በላይ ሰብል ይጠበቃል

Nov 10, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ገንዳ ወሃ፤ ጥቅምት 29/2018(ኢዜአ)፡ - በምዕራብ ጎንደር ዞን በበጋ መስኖ ከሚለማው መሬት ከ700 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት መታቀዱን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

በዞኑ በበጋ መስኖ ልማት እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን የሚደግፍ የመስክ ምልከታ ተካሄዷል።

የመምሪያው ምክትል ኃላፊ አቶ ጤናው ፋንታሁን፣ ዞኑ በመስኖ መልማት የሚችል ሰፊ መሬትና የውኃ አቅም መኖሩን አመላክተዋል።

ይሁን እንጅ በመስኖ ልማት የሚሳተፉ አርሶ አደሮችና የሚሸፈነው መሬት ዞኑ ባለው እምቅ ሀብት ልክ አለመሆኑን ተናግረዋል።

በዚህ አመት ከ3 ሺህ 200 ሄክታር በላይ መሬት በአትክልት፣ ፍራፍሬና አዝዕርት የሚለማ መሆኑን ገልፀው በዚህም ከ700 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።


በዞኑ ሽንኩርት፣ ቲማቲም፣ ፓፓያ፣ ሎሚ፣ ሙዝ እና ሌሎችም የአትክልትና ፍራፍሬ አይነቶች በብዛት የሚመረቱ ሲሆን በቆሎና የበጋ መስኖ ስንዴም የሚለማ መሆኑን ገልፀዋል።

በበጋ መስኖ ልማት ከሚሳተፉ አርሶአደሮች መካከል አርሶአደር ሙሀመድ ገደፋው እንዳሉት በአንድ ሄክታር መሬት ላይ ሽንኩርት፣ ቲማቲምና ጎመን ለማልማት አቅደዋል ።


እስካሁን ሩብ ሄክታር የሚሆነውን በዘር መሸፈናቸውን ገልፀው በቀጣይ እቅዳቸውን ለማሳካት ጥረታቸውን እንደሚቀጥሉ አብራርተዋል።

ሌላኛው አርሶአደር አደም ሁሴን በበኩላቸው በአንድ ሄክታር ከግማሽ በሆነ መሬት ላይ ቋሚ አትክልትና ፍራፍሬን ጨምሮ አዝዕርት ሰብሎች የሚያለሙ መሆኑን ተናግረዋል።


ቋሚ የፍራፍሬ ችግኞችን ከግብርና በማግኘቴ ፓፓያና ማንጎ እያለማሁ ነው ያሉት አርሶአደሩ ፓፓያው ደስ በሚያሰኝ መልኩ ማፍራት መጀመሩን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025