የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በምዕራብ ጎንደር ዞን በበጋ መስኖ ከሚለማው መሬት ከ700 ሺህ ኩንታል በላይ ሰብል ይጠበቃል

Nov 10, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ገንዳ ወሃ፤ ጥቅምት 29/2018(ኢዜአ)፡ - በምዕራብ ጎንደር ዞን በበጋ መስኖ ከሚለማው መሬት ከ700 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት መታቀዱን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

በዞኑ በበጋ መስኖ ልማት እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን የሚደግፍ የመስክ ምልከታ ተካሄዷል።

የመምሪያው ምክትል ኃላፊ አቶ ጤናው ፋንታሁን፣ ዞኑ በመስኖ መልማት የሚችል ሰፊ መሬትና የውኃ አቅም መኖሩን አመላክተዋል።

ይሁን እንጅ በመስኖ ልማት የሚሳተፉ አርሶ አደሮችና የሚሸፈነው መሬት ዞኑ ባለው እምቅ ሀብት ልክ አለመሆኑን ተናግረዋል።

በዚህ አመት ከ3 ሺህ 200 ሄክታር በላይ መሬት በአትክልት፣ ፍራፍሬና አዝዕርት የሚለማ መሆኑን ገልፀው በዚህም ከ700 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።


በዞኑ ሽንኩርት፣ ቲማቲም፣ ፓፓያ፣ ሎሚ፣ ሙዝ እና ሌሎችም የአትክልትና ፍራፍሬ አይነቶች በብዛት የሚመረቱ ሲሆን በቆሎና የበጋ መስኖ ስንዴም የሚለማ መሆኑን ገልፀዋል።

በበጋ መስኖ ልማት ከሚሳተፉ አርሶአደሮች መካከል አርሶአደር ሙሀመድ ገደፋው እንዳሉት በአንድ ሄክታር መሬት ላይ ሽንኩርት፣ ቲማቲምና ጎመን ለማልማት አቅደዋል ።


እስካሁን ሩብ ሄክታር የሚሆነውን በዘር መሸፈናቸውን ገልፀው በቀጣይ እቅዳቸውን ለማሳካት ጥረታቸውን እንደሚቀጥሉ አብራርተዋል።

ሌላኛው አርሶአደር አደም ሁሴን በበኩላቸው በአንድ ሄክታር ከግማሽ በሆነ መሬት ላይ ቋሚ አትክልትና ፍራፍሬን ጨምሮ አዝዕርት ሰብሎች የሚያለሙ መሆኑን ተናግረዋል።


ቋሚ የፍራፍሬ ችግኞችን ከግብርና በማግኘቴ ፓፓያና ማንጎ እያለማሁ ነው ያሉት አርሶአደሩ ፓፓያው ደስ በሚያሰኝ መልኩ ማፍራት መጀመሩን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026