🔇Unmute
ባህር ዳር፤ ሕዳር 1/2018(ኢዜአ)፡-በባህር ዳር ከተማ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ሥራ የከተማዋን ጽዳትና ውበት ይበልጥ ከማሳደጉ ባለፈ የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት መስህብነቷ እንዲጨምር ማስቻሉን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።
የአስተዳደሩ ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ወንዳለ ጋሻው እንዳሉት፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢንሼቲቭ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ሥራ ለከተማዋ እድገት ዘርፈ ብዙ ዕድል ይዞ መጥቷል።
ባህር ዳር በተፈጥሮ ውብ ከተማ ብትሆንም በኮሪደር ልማቱ ያላትን ውበት ይበልጥ ከፍ ያደረጉ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል።
እንደ አቶ ወንዳለ ገለጻ የከተማዋን ነዋሪዎችና ባለሀብቱን በማስተባበር 22 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ሥራ ለማከናወን ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል።
እስካሁን በተደረገ ጥረትም በመጀመሪያው ምዕራፍ በከተማው ከአጂፕ እስከ ቀድሞው ጊዮን ሆቴል 3 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ሥራ በማከናወን ለማጠናቀቅ ተችሏል ብለዋል።

በሁለተኛው ምዕራፍ ከአልማ እስከ ዋተር ፍሮንት ደረጃውን የጠበቀ የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነ ሲሆን አፈጻጸሙም በጥሩ ሂደት ላይ እንደሚገኝ ነው የገለጹት።
ለመጀመሪያውና ሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ ከ3 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ መደረጉን ጠቁመው፣ ለልማት ሥራው ማህበረሰቡ በተለያየ መንገድ እያደረገ ያለው ድጋፍ ከፍተኛ ነው ብለዋል።
በሦስተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ ከጣና ማሪና እስከ ዘጌ መገንጠያ ድረስ 4 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የልማት ሥራ እንደሚከናወንና በአሁኑ ወቅትም ልማቱ የሚነካቸው አካባቢዎችን ከሦስተኛ ወገን የማፅዳት ሥራ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።
የልማት ሥራውን በፍጥነት ለማከናወን የሥራ ተቋራጭና አማካሪ ድርጅቶችን የመለየት ሥራ መከናወኑንም አቶ ወንዳለ ተናግረዋል።

የኮሪደር ልማቱ የመኪና እና የእግረኛ መንገድ፣ የአረንጓዴና የመዝናኛ ስፍራ እንዲሁም የብስክሌት መንገድና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን አካቶ በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
የኮሪደር ልማቱ ባህር ዳር ከተማን ይበልጥ ውብ፣ ፅዱና ማራኪ እያደረጋት መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም የቱሪስት መስህብነቷን ከመጨመር ባለፈ ለኢንቨስትመንትና ለነዋሪዎቿ ምቹ እንዳደረጋት አመልክተዋል።
የኮሪደር ልማቱ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት በመጨረስ፣ የሥራ ባህልን በመቀየር እና የተቋማትን ቅንጅታዊ አሰራር በማጠናከር መልካም ተሞክሮ የተገኘበት ነው ሲሉም አቶ ወንዳለ ገልጸዋል።
ማህበረሰቡ ለልማቱ በገንዘብ፣ በእውቀትና በተለያየ መንገድ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥልም አቶ ወንዳለ ጠይቀዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026