🔇Unmute
ባህር ዳር፤ ሕዳር 1/2018(ኢዜአ)፡-በባህር ዳር ከተማ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ሥራ የከተማዋን ጽዳትና ውበት ይበልጥ ከማሳደጉ ባለፈ የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት መስህብነቷ እንዲጨምር ማስቻሉን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።
የአስተዳደሩ ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ወንዳለ ጋሻው እንዳሉት፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢንሼቲቭ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ሥራ ለከተማዋ እድገት ዘርፈ ብዙ ዕድል ይዞ መጥቷል።
ባህር ዳር በተፈጥሮ ውብ ከተማ ብትሆንም በኮሪደር ልማቱ ያላትን ውበት ይበልጥ ከፍ ያደረጉ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል።
እንደ አቶ ወንዳለ ገለጻ የከተማዋን ነዋሪዎችና ባለሀብቱን በማስተባበር 22 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ሥራ ለማከናወን ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል።
እስካሁን በተደረገ ጥረትም በመጀመሪያው ምዕራፍ በከተማው ከአጂፕ እስከ ቀድሞው ጊዮን ሆቴል 3 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ሥራ በማከናወን ለማጠናቀቅ ተችሏል ብለዋል።

በሁለተኛው ምዕራፍ ከአልማ እስከ ዋተር ፍሮንት ደረጃውን የጠበቀ የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነ ሲሆን አፈጻጸሙም በጥሩ ሂደት ላይ እንደሚገኝ ነው የገለጹት።
ለመጀመሪያውና ሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ ከ3 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ መደረጉን ጠቁመው፣ ለልማት ሥራው ማህበረሰቡ በተለያየ መንገድ እያደረገ ያለው ድጋፍ ከፍተኛ ነው ብለዋል።
በሦስተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ ከጣና ማሪና እስከ ዘጌ መገንጠያ ድረስ 4 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የልማት ሥራ እንደሚከናወንና በአሁኑ ወቅትም ልማቱ የሚነካቸው አካባቢዎችን ከሦስተኛ ወገን የማፅዳት ሥራ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።
የልማት ሥራውን በፍጥነት ለማከናወን የሥራ ተቋራጭና አማካሪ ድርጅቶችን የመለየት ሥራ መከናወኑንም አቶ ወንዳለ ተናግረዋል።

የኮሪደር ልማቱ የመኪና እና የእግረኛ መንገድ፣ የአረንጓዴና የመዝናኛ ስፍራ እንዲሁም የብስክሌት መንገድና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን አካቶ በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
የኮሪደር ልማቱ ባህር ዳር ከተማን ይበልጥ ውብ፣ ፅዱና ማራኪ እያደረጋት መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም የቱሪስት መስህብነቷን ከመጨመር ባለፈ ለኢንቨስትመንትና ለነዋሪዎቿ ምቹ እንዳደረጋት አመልክተዋል።
የኮሪደር ልማቱ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት በመጨረስ፣ የሥራ ባህልን በመቀየር እና የተቋማትን ቅንጅታዊ አሰራር በማጠናከር መልካም ተሞክሮ የተገኘበት ነው ሲሉም አቶ ወንዳለ ገልጸዋል።
ማህበረሰቡ ለልማቱ በገንዘብ፣ በእውቀትና በተለያየ መንገድ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥልም አቶ ወንዳለ ጠይቀዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026