የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የባህር ዳር ከተማ የኮሪደር ልማት የከተማዋ የቱሪዝም መስህብነት እንዲጨምር አድርጓል

Nov 10, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ ሕዳር 1/2018(ኢዜአ)፡-በባህር ዳር ከተማ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ሥራ የከተማዋን ጽዳትና ውበት ይበልጥ ከማሳደጉ ባለፈ የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት መስህብነቷ እንዲጨምር ማስቻሉን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።

የአስተዳደሩ ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ወንዳለ ጋሻው እንዳሉት፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢንሼቲቭ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ሥራ ለከተማዋ እድገት ዘርፈ ብዙ ዕድል ይዞ መጥቷል።

ባህር ዳር በተፈጥሮ ውብ ከተማ ብትሆንም በኮሪደር ልማቱ ያላትን ውበት ይበልጥ ከፍ ያደረጉ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል።

እንደ አቶ ወንዳለ ገለጻ የከተማዋን ነዋሪዎችና ባለሀብቱን በማስተባበር 22 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ሥራ ለማከናወን ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል።

እስካሁን በተደረገ ጥረትም በመጀመሪያው ምዕራፍ በከተማው ከአጂፕ እስከ ቀድሞው ጊዮን ሆቴል 3 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ሥራ በማከናወን ለማጠናቀቅ ተችሏል ብለዋል።


በሁለተኛው ምዕራፍ ከአልማ እስከ ዋተር ፍሮንት ደረጃውን የጠበቀ የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነ ሲሆን አፈጻጸሙም በጥሩ ሂደት ላይ እንደሚገኝ ነው የገለጹት።

ለመጀመሪያውና ሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ ከ3 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ መደረጉን ጠቁመው፣ ለልማት ሥራው ማህበረሰቡ በተለያየ መንገድ እያደረገ ያለው ድጋፍ ከፍተኛ ነው ብለዋል።

በሦስተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ ከጣና ማሪና እስከ ዘጌ መገንጠያ ድረስ 4 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የልማት ሥራ እንደሚከናወንና በአሁኑ ወቅትም ልማቱ የሚነካቸው አካባቢዎችን ከሦስተኛ ወገን የማፅዳት ሥራ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

የልማት ሥራውን በፍጥነት ለማከናወን የሥራ ተቋራጭና አማካሪ ድርጅቶችን የመለየት ሥራ መከናወኑንም አቶ ወንዳለ ተናግረዋል።


የኮሪደር ልማቱ የመኪና እና የእግረኛ መንገድ፣ የአረንጓዴና የመዝናኛ ስፍራ እንዲሁም የብስክሌት መንገድና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን አካቶ በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

የኮሪደር ልማቱ ባህር ዳር ከተማን ይበልጥ ውብ፣ ፅዱና ማራኪ እያደረጋት መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም የቱሪስት መስህብነቷን ከመጨመር ባለፈ ለኢንቨስትመንትና ለነዋሪዎቿ ምቹ እንዳደረጋት አመልክተዋል።

የኮሪደር ልማቱ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት በመጨረስ፣ የሥራ ባህልን በመቀየር እና የተቋማትን ቅንጅታዊ አሰራር በማጠናከር መልካም ተሞክሮ የተገኘበት ነው ሲሉም አቶ ወንዳለ ገልጸዋል።

ማህበረሰቡ ለልማቱ በገንዘብ፣ በእውቀትና በተለያየ መንገድ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥልም አቶ ወንዳለ ጠይቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026