የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በኢትዮጵያ ኢንተርፕርነርሽፕን የመንግስት መለያ ማድረግ የሚያስችሉ ተቋማትና ሕጎች ተተግብረዋል - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል

Nov 20, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ህዳር 8/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት ኢንተርፕርነርሽፕን የመንግስት መለያ ማድረግ የሚያስችሉ ተቋማትና ሕጎች መተግበራቸውን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ።

የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ጠባቂነትን አስወግዶ በሀሳብ ሀብት መፍጠር እንደሚቻል ያሳየ ተቋም መሆኑንም ጠቅሰዋል።

የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴርና ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት በኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት "በጋራ እንገንባ" በሚል መሪ ሀሳብ ተከፍቷል።

የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሀሰን ሁሴን(ዶ/ር)፣ ዲፕሎማቶችና ሌሎች ተሳታፊዎች በመክፈቻ መርሀ ግብር ላይ ተገኝተዋል።

ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በዓለም አደባባይ ስሟን ከፍ ያደረጉ አንቱ የተባሉ ምስጉን፣ ታታሪ ኢንተርፕርነሮችስ ስትፈጥር ቆይታለች።


ይሁን እንጂ ኢትዮጵያ ኢንተርፕርነርሽፕን የመንግስቷ መለያ ማድረግ የሚያስችሉ ተቋማትን የገነባችው፣ ሕጎችን ያወጣችው ባለፉት ሰባት ዓመታት ነው ብለዋል።

በተለይም ባለፉት አራት ዓመታት የኢንተርፕርነርሽፕ ሥነ ምህዳርን ተቋማዊ ማድረግ የሚያስችል እንቅስቃሴ መደረጉን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ የሀሳብ ብዝሃነት ጸጋ ለሀሳብ ፈጠራ ወሳኝ መሆኑን በማንሳት፤ የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ጠባቂነትን አስወግዶ በሀሳብ ሀብት መፍጠር እንደሚቻል በተግባር አሳይቷል ነው ያሉት።

በዚህም ባለፉት ሰባት ዓመታት በኢትዮጵያ ኢንተርፕርነርሽፕን የመንግስት መለያ ማድረግ የሚያስችሉ ተቋማትና ሕጎች ተተግብረዋል ብለዋል።

ኢትዮጵያ የኢንተርፕርነሮች መፍለቂያ ትሆናለች ያሉት ሚኒስትሯ፤ መንግሥት የኢንተርፕርነርሽፕ ምህዳሩን ምቹ ማድረጉን ገልጸዋል።

ሀሳብ ካለ ሀብት መፍጠር እንደሚቻል አምናለሁ ያሉት ሚኒስትሯ፤ ይህን ተግባራዊ ማድረግ የሚያስችል እምቅ ሀገራዊ አቅም፣ ፖሊሲና ተቋም ተገንብቷልም ብለዋል።

የመደመር መንግሥት ኢትዮጵያ ኢንተርፕርነር መሆንና እንዴት እንደምትሆን በግልጽ አስቀምጧል ነው ያሉት።


የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሀሰን ሁሴን(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ የኢንተርፕርነርሽፕ ሁነቶችን በማዘጋጀት ብራዚልን በመቅደም ከዓለም አንደኛ ሆናለች ብለዋል።

ኢንተርፕርነሮች የፈጠራ መፍትሔዎችን ወደ መሬት የሚቀይሩ፣ ምኞትን የሚያሳኩ፣ አይቻልምን ችለው የሚያሳዩ ፈር ቀዳጅ ባለራዕዮችና ከዋኞች ናቸው ነው ያሉት።

ኢንተርፕርነሮች ሀገር ሰሪዎች መሆናቸውን ጠቁመውም በዘንድሮው 12ኛው የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት ስልጠናዎች፣ የፈጠራ ሀሳብ ውድድሮችና ጥናቶች ይከናወናሉ ብለዋል።

በኢትዮጵያ የሚወሰን ሳይሆን ድንበር ተሻጋሪ ሥራ ጀምረናል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ የመጨረሻ ግባችን አይበገሬ ማህበረሰብ፣ ዜጋና ሀገር መገንባት ነው ሲሉም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026