የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

አርሶ አደሮች በሻይ ልማት ስራ ይበልጥ ውጤታማ ለመሆን እየሰሩ ነው

Nov 20, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

መቱ ፤ሕዳር 10/2018 (ኢዜአ)፡- በማህበር ተደራጅተው በጀመሩት የሻይ ልማት ስራ ይበልጥ ውጤታማ ለመሆን እየሰሩ መሆኑን የኢሉአባቦር ዞን አርሶ አደሮች ገለጹ።

የዛሬ ሶስት ዓመት በማህበር ተደራጅተው የተከሉት ሻይ ደርሶ ለፋብሪካ ማቅረብ መጀመራቸውንም አርሶ አደሮቹ ተናግረዋል።

ከአርሶ አደሮቹ መካከል አቶ ታዬ ገብሬ እንዳሉት፤ ስራው በአጭር ጊዜ ለውጤት ይበቃል የሚል እምነት እንዳልነበራቸው አንስተው አሁን ለዚህ ደረጃ በቅቶ በማየታቸው ተነሳሽነታቸው ጨምሯል።


ዛሬ ላይ ለለቀማ ደርሶ ምርቱን በአካባቢያቸው ለሚገኘው ጉመሮ ሻይ ፋብሪካ ማስረከብ በመጀመራቸው ስራውን የበለጠ በማስፋት ተጠቃሚ ለመሆን መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።

አርሶ አደር ከድር ጀማል በበኩላቸው የሻይ ልማት ስራቸው ውጤታማ በመሆኑ በቀጣይ በልዩ ትኩረት ስራውን ለማስፋፋት መዘጋጀታቸውን ጠቅሰዋል።


የግብርና ባለሙያዎች በሻይ ልማት ላይ ከቅድመ ዝግጅቱ ጀምሮ በችግኝ እና በማዳበሪያ አቅርቦት ሲያግዟቸው እንደነበረም አስታውሰዋል።

አቶ ምትኩ አስፋው እና አቶ ፍራኦል ጫንያለው የተባሉ አርሶ አደሮችም እንዲሁ ለሻይ ልማቱ አስፈላጊውን እንክብካቤ ሲያደርጉ መቆየታቸውን ገልጸው በጽናት የሚሰራ ስራ ሁሌም ውጤት እንደሚኖረው አይተንበታል ብለዋል።


አሁን ላይ የደረሰውን የሻይ ቅጠል ከጉመሮ ሻይ ፋብሪካ ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ማስረከብ በመጀመራቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል።

የጉማሮ ሻይ ቅጠል ፋብሪካ ስራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን ምትኩ በበኩላቸው ፋብሪካው የሻይ ቅጠሉን የሚረከበው አስፈላጊውን የማጓጓዣ አቅርቦት እና ባለሙያ በመመደብ መሆኑን ተናግረዋል።

ከዋጋ ጋር በተያያዘ የማምረቻ ወጪያቸውንና በገበያ ላይ ያለውን ተለዋዋጭና ተጨባጭ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ በየዓመቱ በሚታደስ ውል ምርቱን የሚቀበሉ መሆናቸውንም አንስተዋል።

በዚህም አርሶ አደሩና ድርጅቱ በጋራ ተጠቃሚ በሚሆኑበት ሁኔታ ላይ በዘላቂነት እንደሚሰራ ገልጸዋል።


በኢሉባቦር ዞን ባለፉት ዓመታት ለሻይ ልማት ስራ በተሰጠው ትኩረት በስምንት ወረዳዎች የልማት ስራው መጀመሩን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ቻላቸው አዱኛ ተናግረዋል።

በአጠቃላይ በዞኑ ከ1 ሺህ 600 ሔክታር በላይ መሬት በሻይ እየለማ መሆኑን ገልጸው ከዚህም ውስጥ 573 ሔክታር ያህሉ በአርሶ አደሮች የለማ ነው ብለዋል።

ባለፉት ዓመታት በኩታ ገጠም ከለማው ሻይም በ300 ሔክታር መሬት ላይ በሶስት ማህበራት የተተከለው ሻይ ለለቀማ በመድረሱ ከጉመሮ ሻይ ፋብሪካ ጋር የገበያ ትስስር ተፈጥሮ ወደ ለቀማ መገባቱንም አስታውሰዋል።

በቀጣይም የሻይ ልማት ስራውን ከማስፋፋት ጎን ለጎን ማህበራቱ የሻይ ቅጠል ማቀነባበሪያ ፋብሪካ እንዲኖራቸው የማድረግ ስራ እንደሚሰራም አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026