🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሕዳር 10/2018 (ኢዜአ)፡-በኢትዮጵያ ያሉ የኢንቨስትመንት አማራጮችን በማስተዋወቅ ባለሃብቶችን ለመሳብና የንግድ ትስስሩን ለማጠናከር የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በተለያዩ ሀገራት የሚገኙ የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች ገለፁ።
በተለያዩ አገራት ያሉ የኢትዮጵያ አምባሳደሮች ለኢዜአ እንዳሉት የኢትዮጵያን ምርቶች በማስተዋወቅ በአለም ገበያ ያላቸውን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ።
በኩዌት የኢትዮጵያ ኤምባሲ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሰኢድ መሀመድ(ዶ/ር) ፤ኩዌት የኢትዮጵያ ስትራቴጂክ አጋርና በስራ ስምሪት መዳረሻ ከሆኑ አገራት አንዷ መሆኗን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያን የስጋ፣ ቡና፣ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶች በኩዌት ገበያ የማስተዋወቅ ስራዎች መጀመራቸውን ገልፀው በቀጣይ በርካታ የኢትዮጵያ ምርቶች በኩዌት ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የሚረዱ ተግባራት ይከናወናሉ ብለዋል።
ምርቶቹን በኩዌት ገበያ በስፋት ለማስተዋወቅና የሁለቱ አገራት ንግድ ምክር ቤቶች አስፈላጊ ስራዎችን በጋራ እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል።
በኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ የኩዌት ባለሃብቶች ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ኢንቨስት እንዲያደርጉ የሚረዱ ተግባራት መጀመራቸውን አስታውቀው የአገራቱን የኢኮኖሚ ትስስር ለማጠናከር በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል ።
አሁን ላይ 22 የኩዌት ባለሃብቶች በኢትዮጵያ መሰማራታቸውን አንስተው ስትራቴጂክ ኩባንያዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ ለማድረግ ድርድሮች መጀመራቸውን ነው የገለፁት።
በእንግሊዝ እና ሰሜን አየርላንድ የኢትዮጵያ አምባሳደር ብሩክ መኮንን፤ በኤምባሲው የቢዝነስ ማስተዋወቂያ ፎረሞችን በማዘጋጀትና መድረኮችን በመጠቀም ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያንም በተለዩ የትኩረት መስኮች እንዲሰማሩ ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል።
የኢኮኖሚ ሪፎርሙን ተከትሎ በአካባቢዎቹ ያለው የቢዝነስ ኮሙዩኒቲ በኢትዮጵያ ኢንቨስት ለማድረግ ፍላጎት እንዳለው አይተናል ብለዋል።
በቅርቡ የኢትዮጵያና የታላቋ ብሪታንያ የንግድ ምክር ቤት መቋቋሙንና የመጀመሪያ የማስተዋወቂያ መድረክ በለንደን መካሄዱን አንስተዋል።
በቀጣይም የቢዝነስ ልዑክ ቡደኑ ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት የማስተዋወቂያ ፎረም እንደሚካሄድ ነው የጠቆሙት።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026