🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሕዳር 10/2018 (ኢዜአ)፡-በኢትዮጵያ ያሉ የኢንቨስትመንት አማራጮችን በማስተዋወቅ ባለሃብቶችን ለመሳብና የንግድ ትስስሩን ለማጠናከር የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በተለያዩ ሀገራት የሚገኙ የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች ገለፁ።
በተለያዩ አገራት ያሉ የኢትዮጵያ አምባሳደሮች ለኢዜአ እንዳሉት የኢትዮጵያን ምርቶች በማስተዋወቅ በአለም ገበያ ያላቸውን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ።
በኩዌት የኢትዮጵያ ኤምባሲ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሰኢድ መሀመድ(ዶ/ር) ፤ኩዌት የኢትዮጵያ ስትራቴጂክ አጋርና በስራ ስምሪት መዳረሻ ከሆኑ አገራት አንዷ መሆኗን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያን የስጋ፣ ቡና፣ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶች በኩዌት ገበያ የማስተዋወቅ ስራዎች መጀመራቸውን ገልፀው በቀጣይ በርካታ የኢትዮጵያ ምርቶች በኩዌት ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የሚረዱ ተግባራት ይከናወናሉ ብለዋል።
ምርቶቹን በኩዌት ገበያ በስፋት ለማስተዋወቅና የሁለቱ አገራት ንግድ ምክር ቤቶች አስፈላጊ ስራዎችን በጋራ እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል።
በኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ የኩዌት ባለሃብቶች ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ኢንቨስት እንዲያደርጉ የሚረዱ ተግባራት መጀመራቸውን አስታውቀው የአገራቱን የኢኮኖሚ ትስስር ለማጠናከር በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል ።
አሁን ላይ 22 የኩዌት ባለሃብቶች በኢትዮጵያ መሰማራታቸውን አንስተው ስትራቴጂክ ኩባንያዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ ለማድረግ ድርድሮች መጀመራቸውን ነው የገለፁት።
በእንግሊዝ እና ሰሜን አየርላንድ የኢትዮጵያ አምባሳደር ብሩክ መኮንን፤ በኤምባሲው የቢዝነስ ማስተዋወቂያ ፎረሞችን በማዘጋጀትና መድረኮችን በመጠቀም ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያንም በተለዩ የትኩረት መስኮች እንዲሰማሩ ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል።
የኢኮኖሚ ሪፎርሙን ተከትሎ በአካባቢዎቹ ያለው የቢዝነስ ኮሙዩኒቲ በኢትዮጵያ ኢንቨስት ለማድረግ ፍላጎት እንዳለው አይተናል ብለዋል።
በቅርቡ የኢትዮጵያና የታላቋ ብሪታንያ የንግድ ምክር ቤት መቋቋሙንና የመጀመሪያ የማስተዋወቂያ መድረክ በለንደን መካሄዱን አንስተዋል።
በቀጣይም የቢዝነስ ልዑክ ቡደኑ ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት የማስተዋወቂያ ፎረም እንደሚካሄድ ነው የጠቆሙት።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026