የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ኢትዮጵያ ከተለያዩ ሀገራት ጋር ያላትን የንግድ ትስስር ለማጠናከር የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

Nov 20, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሕዳር 10/2018 (ኢዜአ)፡-በኢትዮጵያ ያሉ የኢንቨስትመንት አማራጮችን በማስተዋወቅ ባለሃብቶችን ለመሳብና የንግድ ትስስሩን ለማጠናከር የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በተለያዩ ሀገራት የሚገኙ የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች ገለፁ።

በተለያዩ አገራት ያሉ የኢትዮጵያ አምባሳደሮች ለኢዜአ እንዳሉት የኢትዮጵያን ምርቶች በማስተዋወቅ በአለም ገበያ ያላቸውን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ።

በኩዌት የኢትዮጵያ ኤምባሲ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሰኢድ መሀመድ(ዶ/ር) ፤ኩዌት የኢትዮጵያ ስትራቴጂክ አጋርና በስራ ስምሪት መዳረሻ ከሆኑ አገራት አንዷ መሆኗን ተናግረዋል።


የኢትዮጵያን የስጋ፣ ቡና፣ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶች በኩዌት ገበያ የማስተዋወቅ ስራዎች መጀመራቸውን ገልፀው በቀጣይ በርካታ የኢትዮጵያ ምርቶች በኩዌት ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የሚረዱ ተግባራት ይከናወናሉ ብለዋል።

ምርቶቹን በኩዌት ገበያ በስፋት ለማስተዋወቅና የሁለቱ አገራት ንግድ ምክር ቤቶች አስፈላጊ ስራዎችን በጋራ እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል።

በኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ የኩዌት ባለሃብቶች ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ኢንቨስት እንዲያደርጉ የሚረዱ ተግባራት መጀመራቸውን አስታውቀው የአገራቱን የኢኮኖሚ ትስስር ለማጠናከር በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል ።

አሁን ላይ 22 የኩዌት ባለሃብቶች በኢትዮጵያ መሰማራታቸውን አንስተው ስትራቴጂክ ኩባንያዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ ለማድረግ ድርድሮች መጀመራቸውን ነው የገለፁት።

በእንግሊዝ እና ሰሜን አየርላንድ የኢትዮጵያ አምባሳደር ብሩክ መኮንን፤ በኤምባሲው የቢዝነስ ማስተዋወቂያ ፎረሞችን በማዘጋጀትና መድረኮችን በመጠቀም ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።


ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያንም በተለዩ የትኩረት መስኮች እንዲሰማሩ ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል።

የኢኮኖሚ ሪፎርሙን ተከትሎ በአካባቢዎቹ ያለው የቢዝነስ ኮሙዩኒቲ በኢትዮጵያ ኢንቨስት ለማድረግ ፍላጎት እንዳለው አይተናል ብለዋል።

በቅርቡ የኢትዮጵያና የታላቋ ብሪታንያ የንግድ ምክር ቤት መቋቋሙንና የመጀመሪያ የማስተዋወቂያ መድረክ በለንደን መካሄዱን አንስተዋል።

በቀጣይም የቢዝነስ ልዑክ ቡደኑ ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት የማስተዋወቂያ ፎረም እንደሚካሄድ ነው የጠቆሙት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026