🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሕዳር 10/2018 (ኢዜአ)፡-የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ ንግድ ቀጣና የጥራጥሬና ቅባት እህሎችን የገበያ መዳረሻ በማስፋት የላኪዎችን ተወዳዳሪነት ለማጠናከር ያስችላል ሲሉ የኢትዮጵያ ጥራጥሬና ቅባት እህሎች ላኪዎች ማህበር ፕሬዝዳንት አቶ ኤዳኦ አብዲ ገለፁ።
ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ ንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራን መስከረም 29 ቀን 2018 ምርቶቿን ወደተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት በመላክ በይፋ መጀመሯ ይታወቃል።
በዚህም ሥጋ፣ አትክልትና ፍራፍሬ፣ ቡና፣ የጥራጥሬ ምርቶችና የቅባት እህሎችን በኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎና በየብስ ትራንስፖርት አማካይነት ወደ ኬንያ፣ ሶማሊያ እና ደቡብ አፍሪካ መላክ ጀምራለች።

የኢትዮጵያ ጥራጥሬና ቅባት እህሎች ላኪዎች ማህበር ፕሬዝዳንት አቶ ኤዳኦ አብዲ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ለዘርፉ ያለውን ጠቀሜታ በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።
ነፃ የንግድ ቀጣናው በአፍሪካ ሰፊ የገበያ ዕድል እንደሚፈጥር ገልጸው፤ ዕድሉ በተለይም የጥራጥሬና የቅባት እህል አምራቾች ምርቶቻቸውን በተሻለ አማራጭ ለገበያ ማቅረብ የሚችሉበትን አዲስና ሰፊ ገበያ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።
ስምምነቱ በአፍሪካ ሀገራት መካከል የተጣሉትን የንግድ ቀረጥና ታሪፎችን ቀስ በቀስ በማስቀረት ለወጪ ንግድ የሚቀርቡ የጥራጥሬና የቅባት እህሎች በአፍሪካ ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ያስችላቸዋል ብለዋል።

የጥራጥሬና ቅባት እህል ላኪ የሆኑት አቶ ዳኛቸው አሰፋ በበኩላቸው፤ ስምምነቱ አዳዲስ የገበያ መዳረሻዎችን በማስፋት እና ተወዳዳሪነትን በመጨመር የጥራጥሬና የቅባት እህሎችን የወጪ ንግድ መጠንና ገቢ ያሳድጋል ብለዋል።

ስምምነቱ ተግባራዊ መደረጉ የአፍሪካን የንግድ ልውውጥ የሚቀይር ነው ያሉት ደግሞ የናይጄሪያ ብሔራዊ የሰሊጥ ዘር ማኅበር ተወካይ እያሱ ይስሃቅ ናቸው።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025