የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ነጻ የንግድ ቀጣናው የላኪዎችን ተወዳዳሪነት ያጠናክራል

Nov 20, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሕዳር 10/2018 (ኢዜአ)፡-የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ ንግድ ቀጣና የጥራጥሬና ቅባት እህሎችን የገበያ መዳረሻ በማስፋት የላኪዎችን ተወዳዳሪነት ለማጠናከር ያስችላል ሲሉ የኢትዮጵያ ጥራጥሬና ቅባት እህሎች ላኪዎች ማህበር ፕሬዝዳንት አቶ ኤዳኦ አብዲ ገለፁ።

ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ ንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራን መስከረም 29 ቀን 2018 ምርቶቿን ወደተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት በመላክ በይፋ መጀመሯ ይታወቃል።

በዚህም ሥጋ፣ አትክልትና ፍራፍሬ፣ ቡና፣ የጥራጥሬ ምርቶችና የቅባት እህሎችን በኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎና በየብስ ትራንስፖርት አማካይነት ወደ ኬንያ፣ ሶማሊያ እና ደቡብ አፍሪካ መላክ ጀምራለች።


የኢትዮጵያ ጥራጥሬና ቅባት እህሎች ላኪዎች ማህበር ፕሬዝዳንት አቶ ኤዳኦ አብዲ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ለዘርፉ ያለውን ጠቀሜታ በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።

ነፃ የንግድ ቀጣናው በአፍሪካ ሰፊ የገበያ ዕድል እንደሚፈጥር ገልጸው፤ ዕድሉ በተለይም የጥራጥሬና የቅባት እህል አምራቾች ምርቶቻቸውን በተሻለ አማራጭ ለገበያ ማቅረብ የሚችሉበትን አዲስና ሰፊ ገበያ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።

ስምምነቱ በአፍሪካ ሀገራት መካከል የተጣሉትን የንግድ ቀረጥና ታሪፎችን ቀስ በቀስ በማስቀረት ለወጪ ንግድ የሚቀርቡ የጥራጥሬና የቅባት እህሎች በአፍሪካ ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ያስችላቸዋል ብለዋል።


የጥራጥሬና ቅባት እህል ላኪ የሆኑት አቶ ዳኛቸው አሰፋ በበኩላቸው፤ ስምምነቱ አዳዲስ የገበያ መዳረሻዎችን በማስፋት እና ተወዳዳሪነትን በመጨመር የጥራጥሬና የቅባት እህሎችን የወጪ ንግድ መጠንና ገቢ ያሳድጋል ብለዋል።


ስምምነቱ ተግባራዊ መደረጉ የአፍሪካን የንግድ ልውውጥ የሚቀይር ነው ያሉት ደግሞ የናይጄሪያ ብሔራዊ የሰሊጥ ዘር ማኅበር ተወካይ እያሱ ይስሃቅ ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025