🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሕዳር 10/2018 (ኢዜአ)፡-የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ ንግድ ቀጣና የጥራጥሬና ቅባት እህሎችን የገበያ መዳረሻ በማስፋት የላኪዎችን ተወዳዳሪነት ለማጠናከር ያስችላል ሲሉ የኢትዮጵያ ጥራጥሬና ቅባት እህሎች ላኪዎች ማህበር ፕሬዝዳንት አቶ ኤዳኦ አብዲ ገለፁ።
ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ ንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራን መስከረም 29 ቀን 2018 ምርቶቿን ወደተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት በመላክ በይፋ መጀመሯ ይታወቃል።
በዚህም ሥጋ፣ አትክልትና ፍራፍሬ፣ ቡና፣ የጥራጥሬ ምርቶችና የቅባት እህሎችን በኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎና በየብስ ትራንስፖርት አማካይነት ወደ ኬንያ፣ ሶማሊያ እና ደቡብ አፍሪካ መላክ ጀምራለች።

የኢትዮጵያ ጥራጥሬና ቅባት እህሎች ላኪዎች ማህበር ፕሬዝዳንት አቶ ኤዳኦ አብዲ፤ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ለዘርፉ ያለውን ጠቀሜታ በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።
ነፃ የንግድ ቀጣናው በአፍሪካ ሰፊ የገበያ ዕድል እንደሚፈጥር ገልጸው፤ ዕድሉ በተለይም የጥራጥሬና የቅባት እህል አምራቾች ምርቶቻቸውን በተሻለ አማራጭ ለገበያ ማቅረብ የሚችሉበትን አዲስና ሰፊ ገበያ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።
ስምምነቱ በአፍሪካ ሀገራት መካከል የተጣሉትን የንግድ ቀረጥና ታሪፎችን ቀስ በቀስ በማስቀረት ለወጪ ንግድ የሚቀርቡ የጥራጥሬና የቅባት እህሎች በአፍሪካ ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ያስችላቸዋል ብለዋል።

የጥራጥሬና ቅባት እህል ላኪ የሆኑት አቶ ዳኛቸው አሰፋ በበኩላቸው፤ ስምምነቱ አዳዲስ የገበያ መዳረሻዎችን በማስፋት እና ተወዳዳሪነትን በመጨመር የጥራጥሬና የቅባት እህሎችን የወጪ ንግድ መጠንና ገቢ ያሳድጋል ብለዋል።

ስምምነቱ ተግባራዊ መደረጉ የአፍሪካን የንግድ ልውውጥ የሚቀይር ነው ያሉት ደግሞ የናይጄሪያ ብሔራዊ የሰሊጥ ዘር ማኅበር ተወካይ እያሱ ይስሃቅ ናቸው።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026