የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የማሌዥያ እና የኢትዮጵያ ግንኙነት የአፍሪካ እና ማሌዢያ ውጤታማ ትብብር ማሳያ ነው - የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም

Nov 21, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ህዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ የማሌዥያ እና የኢትዮጵያ የሁለትዮሽ ግንኙነት የአፍሪካ እና ማሌዢያ ውጤታማ ትብብር ማሳያ ነው ሲሉ የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ጋር ተወያይተዋል።

የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በውይይቱ ወቅት ኢትዮጵያ እና ማሌዢያ የሁለትዮሽ ትብብር እየተጠናከረ መምጣቱን ገልጸዋል።

ማሌዥያውያን ኢትዮጵያ ያላትን ታሪክ በውል እንደሚገነዘቡ ገልጸው ይህም ለሀገራቱ ግንኙነት ልዩ ገጽታ እንደሚሰጠው ተናግረዋል።

ሁለቱ ሀገራት በብሪክስ ማዕቀፍ ያላቸውን ትብብር በማንሳት ማሌዥያ የብሪክስ አጋር ሀገር እንድትሆን ኢትዮጵያ ላደረገችው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።

የሀገራቱ በደቡብ ደቡብ የትብብር ማዕቀፍ ጥሩ ግንኙነት እንዳላቸውም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያነሱት።


በአዲስ አበባ የተካሄደው የኢትዮጵያ እና የማሌዥያ የቢዝነስ ፎረም ለሀገራቱ ትስስር መጠናከር አስተዋጽኦ እንደሚያበረክትም ገልጸዋል።

ማሌዥያ ከኢትዮጵያ ጋር በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በትምህርት፣ በባህል እና ሳይንስን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ያላትን የሁለትዮሽ ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ ናት ብለዋል።

በሌላ በኩል ማሌዥያ አባል የሆነችበት የደቡብ ምስራቅ እስያ ሀገራት ማህበር(ኤስያን) ኢትዮጵያን ጨምሮ በአፍሪካ ገበያ ያላቸውን ተደራሽነት ለማሳደግ ፍላጎት እንዳላቸው አመልክተዋል።

የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ሀገራት መግቢያ በር መሆኗ ማሌዢያ ከኢትዮጵያ ጋር ትብብሯን ማጠናከሯ መልካም አጋጣሚ እንደሚፈጥርላት ነው የገለጹት።

የማሌዥያ እና የኢትዮጵያ ትብብር የማሌዢያ እና የአፍሪካ ውጤታማ ትብብር ማሳያ ነው ሲሉም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026