የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የማሌዥያ እና የኢትዮጵያ ግንኙነት የአፍሪካ እና ማሌዢያ ውጤታማ ትብብር ማሳያ ነው - የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም

Nov 21, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ህዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ የማሌዥያ እና የኢትዮጵያ የሁለትዮሽ ግንኙነት የአፍሪካ እና ማሌዢያ ውጤታማ ትብብር ማሳያ ነው ሲሉ የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ጋር ተወያይተዋል።

የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም በውይይቱ ወቅት ኢትዮጵያ እና ማሌዢያ የሁለትዮሽ ትብብር እየተጠናከረ መምጣቱን ገልጸዋል።

ማሌዥያውያን ኢትዮጵያ ያላትን ታሪክ በውል እንደሚገነዘቡ ገልጸው ይህም ለሀገራቱ ግንኙነት ልዩ ገጽታ እንደሚሰጠው ተናግረዋል።

ሁለቱ ሀገራት በብሪክስ ማዕቀፍ ያላቸውን ትብብር በማንሳት ማሌዥያ የብሪክስ አጋር ሀገር እንድትሆን ኢትዮጵያ ላደረገችው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።

የሀገራቱ በደቡብ ደቡብ የትብብር ማዕቀፍ ጥሩ ግንኙነት እንዳላቸውም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያነሱት።


በአዲስ አበባ የተካሄደው የኢትዮጵያ እና የማሌዥያ የቢዝነስ ፎረም ለሀገራቱ ትስስር መጠናከር አስተዋጽኦ እንደሚያበረክትም ገልጸዋል።

ማሌዥያ ከኢትዮጵያ ጋር በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በትምህርት፣ በባህል እና ሳይንስን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ያላትን የሁለትዮሽ ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ ናት ብለዋል።

በሌላ በኩል ማሌዥያ አባል የሆነችበት የደቡብ ምስራቅ እስያ ሀገራት ማህበር(ኤስያን) ኢትዮጵያን ጨምሮ በአፍሪካ ገበያ ያላቸውን ተደራሽነት ለማሳደግ ፍላጎት እንዳላቸው አመልክተዋል።

የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ሀገራት መግቢያ በር መሆኗ ማሌዢያ ከኢትዮጵያ ጋር ትብብሯን ማጠናከሯ መልካም አጋጣሚ እንደሚፈጥርላት ነው የገለጹት።

የማሌዥያ እና የኢትዮጵያ ትብብር የማሌዢያ እና የአፍሪካ ውጤታማ ትብብር ማሳያ ነው ሲሉም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026