የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የህዝብን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት አጠናክሮ ለማስቀጠል ርብርብ ይደረጋል -አስተዳደሩ

Sep 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

መተማና ሰቆጣ፤ መስከረም 4/2019 (ኢዜአ)፡- የህዝብን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን በላቀ ቅንጅትና ትብብር ለማስቀጠል ርብርብ እንደሚደረግ ተጠቆመ።

በምዕራብ ጎንደር ዞን እና በዋግ ህምራ ብሄረሰብ አስተዳደር የ2018 የበጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም እና የ2019 ዓ.ም እቅድ ትውውቅ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።


የምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እያሱ ይላቅ በገንዳ ውሃ ከተማ እየተካሄደ ባለው መድረክ እንዳሉት፤ ባለፈው የበጀት ዓመት በተደረጉ የተቀናጁ ጥረቶች አስተማማኝ ሰላም በመገንባት አበረታች ውጤት ተመዝግቧል።

ለአካባቢው ሰላምና መረጋጋት መስፈን የህዝቡ ንቁ ተሳትፎና ያልተቋረጠ ድጋፍ ቁልፍ ሚና መጫወቱን ገልፀዋል።

በበጀት ዓመቱ በግብርና ልማት፣ በገቢ አሰባሰብ፣ በከተማ ልማትና በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተሻሉ አፈጻጸሞች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፤ የተገኙ ስኬቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠል በተሻለ መልኩ ርብርብ ይደረጋል ብለዋል።

የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ እንዳለው ማሩ በበኩላቸው፤ ህዝቡ ከመንግስት ጎን በመቆም ላሳየው አበረታች የልማትና የሰላም ፍላጎት ምስጋና አቅርበዋል።


በ2019 የበጀት ዓመት የታቀዱ የልማትና የመልካም አስተዳደር ግቦችን ለማሳካት የፓርቲው አመራርና አባላት ህዝቡን በንቅናቄ በማሳተፍ በቁርጠኝነት እንደሚሰሩም ነው የተናገሩት።

በተመሳሳይ በዋግ-ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር በ2019 በጀት ዓመት የአካባቢን ፀጋ መሰረት ያደረጉ እቅዶችን አቅምን አሟጦ ለመስራት ዝግጅት መደረጉን የገለፁት ደግሞ የሰቆጣ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዳግም ባይነሳኝ ናቸው።


በተጠናቀቀው ዓመት ውስብስብ ችግሮችን በመቋቋም በርካታ የልማት ስኬቶችን ማስመዝገብ መቻሉን አስታውሰው፤ በአዲሱ በጀት ዓመት የተመዘገቡ ስኬቶችን በላቀ ደረጃ ለመፈፀም የሚያስችል አሰራር መዘርጋቱን ተናግረዋል።

የአመራሩን ቅንጅታዊ አሰራር ይበልጥ በማሳደግ ህዝብን ያሳተፉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራትን ማስፋፋት የአዲሱ በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን ገልፀዋል።

በየደረጃው የሚገኙ አስፈፃሚዎችም ተጨባጭና ውጤታማ እቅድ በማቀድና በመፈፀም ለስኬቱ ሊረባረቡ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ለተከታታይ ሶስት ቀናት በሚካሄዱት መድረኮች የወረዳና ከተማ አስተዳደር የስራ ኃላፊዎች ተሳታፊ ሆነዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በዞኑ በምርት ዘመኑ 28 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ የሚያስችሉ ተግባራት እየተካሄዱ ነው

ባህር ዳር፤ መስከረም 4/2019 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ጎንደር ዞን በመኸር ወቅት ከለማው 641 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ከ28 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰ...

Sep 15, 2026

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026