የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ስትራቴጂካዊ አቅምና ሙያዊ ብቃት ለመላው አፍሪካ አርአያ የሚሆን ነው 

Sep 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መስከረም 5/2019 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለፉት አስርት ዓመታት የገነባው ስትራቴጂካዊ ዲሲፕሊን፣የቴክኒክ ልህቀት እና የላቀ ሙያዊ የብቃት ደረጃ ለመላው አፍሪካ አርአያ የሚሆን ነው ሲሉ የቀድሞ የአሜሪካ የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ቲቦር ናጊ ገለጹ።

የአየር መንገዱ ስኬት በመንግስት ባለቤትነት ብቻ የተወሰነ ሳይሆን በሙያዊ ስነምግባርና በገለልተኝነት በመመራቱ ጭምር መሆኑን የቀድሞው ዲፕሎማት ከፐልስ ኦፍ አፍሪካ ጋር ባደረጉት ቆይታ ተናግረዋል።

ተቋሙ በቴክኒክ አቅምና በሰው ኃይል ልማት ላይ ያደረገው ሰፊ ኢንቨስትመንት አሁን ላይ ለደረሰበት ዝና እና ስኬት ቁልፍ ሚና መጫወቱን አመልክተዋል።


አየር መንገዱ ጠንካራ ስትራቴጂ ያለው እና የላቀ የቴክኒክ አቅም የተጎናጸፈ መሆኑን ገልጸው የአውሮፓ አየር መንገዶች አብራሪዎቻቸውን በአዲስ አበባ በሚገኙ ማሰልጠኛዎች (ሲሚውሌተር) ልምምድ እንዲያደርጉ እንደሚልኩ አንስተዋል።

የተቋሙ መካኒኮችም በዓለም ምርጥ ከሆኑት ተርታ እንደሚመደቡ ጠቅሰው መንገደኞች ሁልጊዜም የኢትዮጵያ አየር መንገድን ተመራጭ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።

ዓለም አቀፍ በረራዎች በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ተቋርጠው በነበሩበት አስቸጋሪ ወቅት አየር መንገዱ የላቀ ሙያዊ ብቃት ማሳየቱን ናጊ አስታውሰዋል።

በወቅቱ የቀድሞ የአሜሪካ የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ቲቦር ናጊ በሚያገለግሉበት ወቅት፣ ሌሎች አየር ማረፊያዎች በረራቸውን ባቋረጡበት ጊዜ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ስራ መቀጠሉን ገልጸዋል።

በዚህም ምክንያት አሜሪካ ዜጎቿን ከአፍሪካ ለማስወጣት አየር መንገዱን በስፋት ስትጠቀም እንደነበር በማውሳት የአየር መንገዱን ጽናትና አይበገሬነት አንስተዋል።

የቢሾፍቱን ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ያደነቁ ሲሆን ኢትዮጵያ በአፍሪካ የኢኮኖሚና የአቪዬሽን መሪነት እንድትቀጥል ይህ ፕሮጀክት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።


የአውሮፕላን ማረፊያው ግንባታ የረጅም ጊዜ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ አርቆ አሳቢነት የተሞላበት አካሄድ ነው ብለዋል።

አዲስ አበባ እጅግ ከፍ ያለ ቦታ ላይ መሆኗ ለአንዳንድ አውሮፕላኖች ማረፍና መነሳት አስቸጋሪ መሆኑን በመጥቀስ፣ ይህም የፕሮጀክቱን ስትራቴጂካዊ ፋይዳ የጎላ የሚያደርገው መሆኑን ተናግረዋል።

የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ፕሮጀክት 12.5 ቢሊዮን ዶላር የሚፈጅ ሲሆን፤ ይህ ሜጋ ፕሮጀክት በቢሾፍቱ ከተማ እየተገነባ ይገኛል።

ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያን ይበልጥ የአፍሪካ ግዙፍ የአቪዬሽን ማዕከል የሚያደርጋት ነው።

የኢትዮጵያን አየር መንገድ ስኬት ከረጅም ጊዜ የተቋም ጽናትና ኢንቨስትመንት ጋር የሚቆራኝ ነው ብለዋል።

የቴክኒክ ባለሙያዎች ብቃት፣ስትራቴጂካዊ አስተዳደር እና የመሰረተ ልማት መቀናጀት እንዲሁም የሀገሪቱ ኢኮኖሚ እና የዓለም አቀፍ ትስስር እድገት አየር መንገዱ ያለውን አህጉራዊ ሚና ይበልጥ እንደሚያሳድገው አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በዞኑ በምርት ዘመኑ 28 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ የሚያስችሉ ተግባራት እየተካሄዱ ነው

ባህር ዳር፤ መስከረም 4/2019 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ጎንደር ዞን በመኸር ወቅት ከለማው 641 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ከ28 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰ...

Sep 15, 2026

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026