የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በክልሉ በመኽር ወቅቱ በቅባትና በጥራጥሬ ሰብሎች ከለማው ማሳ ከ34 ነጥብ 3 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል

Sep 18, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህርዳር፤ መስከረም 6/2019 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በመኸር ወቅቱ በቅባትና በጥራጥሬ ሰብሎች ከለማው ማሳ ከ34 ነጥብ 3 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

‎የቢሮው የሰብል ልማትና ጥበቃ ዳይሬክተር ማንደፍሮ አስላከ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በክልሉ በ2018/19 ምርት ዘመን መኸር ወቅት ለውጭ ገበያና ለኢንዱስትሪ ግብዓትነት የሚሆኑ ምርቶችን በብዛትና በጥራት አምርቶ ለማቅረብ እየተሰራ ነው።


‎ለዚህም በመኸር ወቅቱ ከአንድ ሚሊዮን ሄክታር በላይ ማሳ በሰሊጥ፣ በአኩሪ አተር እና ማሾ ሰብሎች ለምቶ እንክብካቤ እየተደረገለት መሆኑን ተናግረዋል።

የኩታ ገጠም አሰራርን መሰረት አድርጎ ከለማው አጠቃላይ ማሳ ውስጥ ከግማሽ ሚሊዮን ሄክታር በላዩ በሰሊጥና ቀሪው ደግሞ በጥራጥሬ ሰብሎች የለማ መሆኑን ጠቅሰዋል።

አሁን ላይ ቡቃያው በጥሩ ቁመና ላይ እንደሚገኝ ጠቁመው አጠቃላይ ከለማው ማሳ ከ34 ነጥብ 3 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ አመላክተዋል።

በሰብል አሰባሰብ ወቅት የምርት ብክነትን ለመቀነስና ጥራቱን ለመጠበቅ ለአርሶ አደሩና ለአልሚ ባለሃብቶች ሙያዊ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል።


‎በምዕራብ ጎንደር ዞን የመተማ ወረዳ ነዋሪ አርሶአደር ንጉሴ አለልኝ፤ በ10 ሄክታር ማሳ ላይ ላለሙት የቅባትና የጥራጥሬ ሰብሎች እንክብካቤ እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል።

አሁን ላይ የሰብሉ ቁመና በጥሩ የእድገት ደረጃ ላይ የሚገኝ በመሆኑ የተሻለ ምርት እንደሚጠብቁ አመላክተዋል።

በምርት ዘመኑ ስምንት ሄክታር ማሳ ላይ ሰሊጥና አኩሪ አተር ማልማታቸውን የገለፁት ደግሞ የወረዳው ነዋሪ አርሶ አደር ወለላው ላቀው ናቸው።

‎ከተያዘው ወር አጋማሽ ጀምሮ የደረሰ ሰሊጥ ስብሰባ እንደሚጀምሩም አመላክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በዞኑ በምርት ዘመኑ 28 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ የሚያስችሉ ተግባራት እየተካሄዱ ነው

ባህር ዳር፤ መስከረም 4/2019 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ጎንደር ዞን በመኸር ወቅት ከለማው 641 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ከ28 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰ...

Sep 15, 2026

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026