የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በአማራ ክልል የተፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በተለያዩ መስኮች ኢንቨስት የሚያደርጉ ባለሀብቶች ቁጥር እየጨመረ ነው

Sep 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህርዳር፤ መስከረም 9/2019 (ኢዜአ)፦ የተፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በክልሉ በተለያዩ መስኮች ኢንቨስት የሚያደርጉ ባለሀብቶች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን የአማራ ክልል የኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ እንድሪስ አብዱ ገለጹ።

የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ እና ሌሎችም የስራ ኃላፊዎች በባሕር ዳር ከተማ የሚገኙ የተለያዩ የኢንዱስትሪ ልማት እንቅስቃሴዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

በጉብኝቱ ወቅት ማብራሪያ የሰጡት የአማራ ክልል የኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ እንድሪስ አብዱ፤ በክልሉ የተፈጠረው አስቻይ ሁኔታ የኢንቨስተሮችን ተሳትፎ እያጠናከረ መምጣቱን ገልጸዋል።


በ2018 በጀት ዓመት ብቻ ከ553 ቢሊዮን ብር በላይ ሀብት ያስመዘገቡ በክልሉ የተለያዩ የኢንቨስትመንት መስኮች ለመሰማራት መግባታቸውን ጠቁመዋል።

በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ ያሉ ማነቆዎችን በመፍታት ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር መቻሉ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ አስችሏል ያሉት ኃላፊው በዚህም ተጨባጭ ውጤት መገኘቱን ተናግረዋል።

በዚህም የክልሉ የአምራች ኢንዱስትሪ ምርታማነት እና የኢንዱስትሪ ዘርፍ እድገት እያሳየ የመጣ መሆኑን ገልጸዋል።

በክልሉ የተፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ኢንቨስት የሚያደርጉ የውጭና የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ቁጥር እየጨመረ ስለመምጣቱም ጠቁመዋል።

በተያዘው በጀት ዓመትም በዘርፉ የሚሰማሩ ኢንቨስተሮችን የመሳብ፣ የዘርፉን እድገትና ምርታማነትን የማስቀጠል ስራ ትኩረት የተሰጠው መሆኑን ተናግረዋል።


የክልሉ ርእሰ መሥተዳድር ጉብኝትም ዋነኛ ዓላማ የኢንዱስትሪዎችን የስራ እንቅስቃሴ በመመልከት ለማበረታታት እና ለችግሮችም የመፍትሄ አቅጣጫ ለማመላከት መሆኑን ገልጸው በዚሁ መሰረት ቀጣይነት ያለው ስራ ይከናወናል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በዞኑ በምርት ዘመኑ 28 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ የሚያስችሉ ተግባራት እየተካሄዱ ነው

ባህር ዳር፤ መስከረም 4/2019 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ጎንደር ዞን በመኸር ወቅት ከለማው 641 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ከ28 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰ...

Sep 15, 2026

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026