የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

አዲስ አበባ በኮሪደርና በወንዝ ዳርቻ ልማት እንደ አዲስ ነው የተወለደችው

Jun 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ በአጭር ጊዜ የተገነቡ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራዎች ከተማዋን አዘምነዋታል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው በመዲናዋ የሚኖሩ የውጭ ሀገራት ዜጎች ገለጹ።

አዲስ አበባ የህብረ ብሔራዊት ኢትዮጵያ ርዕሰ ከተማ፣ የአፍሪካ መዲና፣ የዓለም የዲፕሎማሲ ማዕከል እና የውጭ ዜጎችን ጨምሮ የብዙኃን መኖሪያና የጉብኝት ከተማ ናት።

ይህች ታሪካዊ ከተማ ለወትሮው በአየር ንብረቷ እንጂ በመሰረተ ልማት ዝርጋታዋ በበጎ አትጠቀስም ነበር።

ዛሬ ላይ ግን ያ ታሪክ ተቀይሯል። የለውጡ መንግሥት እንደ አዲስ መልሶ ከገነባቸው ታላላቅ ስኬቶች መካከል አዲስ አበባን እንደ ስሟ ውብ እና ፅዱ ያደረጋት የኮሪደር ልማት ግንባር ቀደሙን ስፍራ ይይዛል።


አዲስ አበባ የአፍሪካ መዲናነቷን ይበልጥ ለማስቀጠልና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለመሆን በሁሉን አቀፍ የለውጥ ጎዳና ላይ ትገኛለች።

ዛሬ ከተማዋ ታሪካዊ ቅርሶቿን ጠብቃ፣ የነዋሪዎቿን የኑሮ ጥራት ባሻሻለ እና የውጭ ዜጎችን ቀልብ በሳበ መልኩ የዘመናዊነት ማማ እየሆነች ነው።

ይህ የመዲናዋ ፈጣን ለውጥ በብዙ የዓለም መሪዎችና በአፍሪካውያን ዘንድ ከፍተኛ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል።

በተለይም በከተማዋ በተለያዩ የሥራ መስኮች ተሰማርተው የሚኖሩ የውጭ ሀገራት ዜጎች የአዲስ አበባን ዕድገትና የዝማኔ ጉዞ በዓይናቸው እያዩት፣ በፈጣን ጊዜ ውስጥ የተሳካ መሆኑ እያስደነቃቸው ነው።

ለወትሮው ይመለከቷቸው የነበሩት ጎስቋላ ሰፈሮች፣ የተቆፋፈሩና ለእግረኛ የማይመቹ መንገዶች ዛሬ እጅግ ዘምነዋል። ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የከተማ መዝናኛ፣ መኖሪያና የሥራ ከባቢም ተፈጥሯል።

በአዲስ አበባ በሚኖሩትና በኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት በአይሲቲ የትምህርት ክፍል መምህር የሆኑት ህንዳዊው ፕሮፌሰር ራቪንድራ ባቡ፣ የከተማዋን ለውጥ ማመን ነው ያቃተኝ፤ ልክ እንደ አዲስ ነው የተወለደችው ሲሉ ነው የገለጹት።


አዲስ አበባን ከለውጥ በፊት፣ የለውጥ ሂደቱንና ከለውጥ በኋላ በአግባቡ እንደተመለከቷት ጠቅሰው፤ በፊት ከሚያውቋት ፍጹም በተለየ መልኩ ወደ ከፍተኛ የዕድገት ጎዳና ተሻግራ በማየታቸው መደነቃቸውን ይናገራሉ።

የከተማዋን ገጽታ የሚያስውቡና ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያላቸው የመሠረተ ልማት ሥራዎች በስፋት መገንባታቸው ለከተማዋ መዘመን ጉልህ አበርክቶ እንዳለው ነው ያነሱት ፕሮፌሰሩ።

ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ጸጋ የታደለች እና ምቹ የሆነ የአየር ጸባይ ያላት ሀገር መሆኗንም ይመሰክራሉ።

በአዲስ አበባ ነዋሪ የሆኑትና በኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የኮንፊሽየስ ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር የሆኑት ቻይናዊው ፓን ሊያንግ፤ የአዲስ አበባ ዕድገት ዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቀ የዘመናዊነት ጉዞ ነው ይላሉ።

የከተማዋ የተቀናጀ የመሠረተ ልማት ዝርጋታ ሲከናወን በቅርበት መመልከታቸውን ጠቅሰው፤ የወንዝ ዳርቻና ሌሎች የልማት ሥራዎች ከተማዋ ውብ እንድትሆን እያደረጓት መሆኑን ይናገራሉ።

አዲስ አበባ በአጭር ዓመታት ያስመዘገበችው ስኬትም የአፍሪካ የዘመናዊነት መሠረትና የፈጣን ልማት ምሳሌ መሆኑን ጠቅሰዋል።


የአዲስ አበባን ገጽታ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከቀየሩ ሜጋ ፕሮጀክቶች መካከል የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ሰፊ የእግረኛ መንገዶች፣ የብስክሌት መንገዶችን፣ አረንጓዴ ስፍራዎችንና ዘመናዊ የመንገድ መብራቶችን፣ ደረጃቸውን የጠበቁ የመኖሪያና የንግድ ስፍራዎችን በማካተት መዲናዋን ወደ ዓለም አቀፍ የዝማኔ ደረጃ አሳድጓታል።

የወንዝ ዳርቻ ልማትም ቀደም ሲል በቆሻሻ የተበከሉ የወንዝ ዳርቻዎችን ወደ ውብ የሕዝብ መዝናኛነት የቀየረ ግዙፍ ፕሮጀክት ነው።

ፕሮፌሰር ራቪንድራ ባቡ እና ፓንሊያንግ እንደሚመሰክሩት የከተማዋ አየር ንብረትና መልክዓ-ምድር ተስማሚ በመሆኑ፣ ከኮሪደርና ከአረንጓዴ ልማት ጋር ተዳምሮ ለቱሪዝምና ለኑሮ እጅግ ተመራጭ አድርጓታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

አዲስ አበባ በኮሪደርና በወንዝ ዳርቻ ልማት እንደ አዲስ ነው የተወለደችው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ በአጭር ጊዜ የተገነቡ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራዎች ከተማዋን አዘምነዋታል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸ...

Jun 23, 2026

በክልሉ የማዕድን ሀብት ልማት ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ አቅም እየሆነ ነው

ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...

Jun 10, 2026

የተጀመረው የብልፅግና ጉዞ የሕዝብን ሀብት ለልማት በማዋል በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...

Jun 9, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...

May 28, 2026