የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የምንገነባው መኖሪያ ቤት ብቻ ሳይሆን ክብራችንን የሚያስጠብቅ ምቹና ፅዱ አካባቢን ነው-ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Jun 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ የምንገነባው መኖሪያ ቤት ብቻ ሳይሆን ክብራችንን የሚያስጠብቅ ምቹና ፅዱ አካባቢን ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በመልዕክታቸው፤ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የዛሬ ሁለት ወር የተጀመረው የቅጠል ተራ የቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት በአስደናቂ ፍጥነት እየተከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

ከንቲባዋ ዛሬ በሳይቱ በመገኘት የግንባታውን ሂደት የገመገሙ ሲሆን፣ የዛሬ ሁለት ወር የተጀመሩት ህንጻዎች በአሁኑ ወቅት 9ኛ ወለል ላይ መድረሳቸውን ተመልክተዋል።


ከቦታ ማጽዳት ስራዎች ጋር በተያያዘ የዛሬ ወር የተጀመሩት ህንጻዎች 4ኛ እና 5ኛ ወለል ላይ የደረሱ ሲሆን፣ ከሁለት ሳምንት በፊት የግንባታ ሂደቱን ከተመለከቱ በኋላ አዲስ የተጨመሩት የሶስት ህንጻዎች ጅማሮም በጥሩ ሂደት ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

በእነዚህ ፕሮጀክቶች የሚገነቡት መኖሪያ ቤቶች ብቻ ሳይሆኑ ለንግድ፣ ለጸጥታ፣ ለትምህርት ቤት እና ለጤና ተቋማት፣ ለስፖርት ማዘዉተሪያ፣ ለህፃናት መጫወቻ እና ለሌሎች ማህበራዊ አገልግሎት መስጫዎች እንዲሁም ለህዝብ የጋራ መገልገያዎች እኩል ትኩረት መሰጠቱን ነው ያብራሩት።

በመሆኑም እየተገነባ ያለው መኖሪያ ቤት ብቻ ሳይሆን ህጻናት ቦርቀው የሚያድጉበት፣ ወጣቶች የአካልና የአዕምሮ ብቃታቸውን የሚያዳብሩበት፣ ዜጎች አገልግሎቶችን በቅርበት የሚያገኙበት እና ክብራቸውን የሚያስጠብቅ ምቹና ፅዱ አካባቢ መሆኑን አመልክተዋል።

በአጠቃላይ የቅጠል ተራ መኖሪያ መንደርን ትናንት ከተጀመረው የገዳም ሰፈር እና በመሀሉ ላይ ከሚገኘው የጣልያን ሰፈር ጋር በማገናኘትና በማልማት፣ አካባቢውን የዘመነ አኗኗርና ሰፊ የስራ እድል የሚፈጥር ስፍራ ለማድረግ መታቀዱንም ነው የገለጹት።

ከንቲባዋ አክለውም በምርጫ ወቅት ላይ ሆኖ የፕሮጀክቶቹ ግንባታ ሳይቀዛቀዝ መቀጠሉ፣ በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ ነዋሪዎችን በታማኝነት የማገልገል አቋማቸው ፅኑ መሆኑን የሚያሳይ መሆኑን ጠቁመዋል።


ህንጻዎቹን በጥራት እና በፍጥነት ገንብተው በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ ሌት ተቀን እየሰሩ የሚገኙ አመራሮችን፣ ሰራተኞችን፣ ማህበራትን፣ ተቋራጮችን እና ሁሉንም ባለድርሻ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ከተረጂነት ለመላቀቅ የተያዘውን ዕቅድ የሚያሳኩ ናቸው

አሶሳ፤ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ከተረጂነት ለመላቀቅ የተያዘውን ዕቅድ የሚያሳኩ ናቸው ሲሉ የቤ...

Jun 24, 2026

አዲስ አበባ በኮሪደርና በወንዝ ዳርቻ ልማት እንደ አዲስ ነው የተወለደችው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ በአጭር ጊዜ የተገነቡ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራዎች ከተማዋን አዘምነዋታል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸ...

Jun 23, 2026

በክልሉ የማዕድን ሀብት ልማት ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ አቅም እየሆነ ነው

ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...

Jun 10, 2026

የተጀመረው የብልፅግና ጉዞ የሕዝብን ሀብት ለልማት በማዋል በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...

Jun 9, 2026