የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የምንገነባው መኖሪያ ቤት ብቻ ሳይሆን ክብራችንን የሚያስጠብቅ ምቹና ፅዱ አካባቢን ነው-ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Jun 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ የምንገነባው መኖሪያ ቤት ብቻ ሳይሆን ክብራችንን የሚያስጠብቅ ምቹና ፅዱ አካባቢን ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በመልዕክታቸው፤ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የዛሬ ሁለት ወር የተጀመረው የቅጠል ተራ የቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት በአስደናቂ ፍጥነት እየተከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

ከንቲባዋ ዛሬ በሳይቱ በመገኘት የግንባታውን ሂደት የገመገሙ ሲሆን፣ የዛሬ ሁለት ወር የተጀመሩት ህንጻዎች በአሁኑ ወቅት 9ኛ ወለል ላይ መድረሳቸውን ተመልክተዋል።


ከቦታ ማጽዳት ስራዎች ጋር በተያያዘ የዛሬ ወር የተጀመሩት ህንጻዎች 4ኛ እና 5ኛ ወለል ላይ የደረሱ ሲሆን፣ ከሁለት ሳምንት በፊት የግንባታ ሂደቱን ከተመለከቱ በኋላ አዲስ የተጨመሩት የሶስት ህንጻዎች ጅማሮም በጥሩ ሂደት ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

በእነዚህ ፕሮጀክቶች የሚገነቡት መኖሪያ ቤቶች ብቻ ሳይሆኑ ለንግድ፣ ለጸጥታ፣ ለትምህርት ቤት እና ለጤና ተቋማት፣ ለስፖርት ማዘዉተሪያ፣ ለህፃናት መጫወቻ እና ለሌሎች ማህበራዊ አገልግሎት መስጫዎች እንዲሁም ለህዝብ የጋራ መገልገያዎች እኩል ትኩረት መሰጠቱን ነው ያብራሩት።

በመሆኑም እየተገነባ ያለው መኖሪያ ቤት ብቻ ሳይሆን ህጻናት ቦርቀው የሚያድጉበት፣ ወጣቶች የአካልና የአዕምሮ ብቃታቸውን የሚያዳብሩበት፣ ዜጎች አገልግሎቶችን በቅርበት የሚያገኙበት እና ክብራቸውን የሚያስጠብቅ ምቹና ፅዱ አካባቢ መሆኑን አመልክተዋል።

በአጠቃላይ የቅጠል ተራ መኖሪያ መንደርን ትናንት ከተጀመረው የገዳም ሰፈር እና በመሀሉ ላይ ከሚገኘው የጣልያን ሰፈር ጋር በማገናኘትና በማልማት፣ አካባቢውን የዘመነ አኗኗርና ሰፊ የስራ እድል የሚፈጥር ስፍራ ለማድረግ መታቀዱንም ነው የገለጹት።

ከንቲባዋ አክለውም በምርጫ ወቅት ላይ ሆኖ የፕሮጀክቶቹ ግንባታ ሳይቀዛቀዝ መቀጠሉ፣ በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ ነዋሪዎችን በታማኝነት የማገልገል አቋማቸው ፅኑ መሆኑን የሚያሳይ መሆኑን ጠቁመዋል።


ህንጻዎቹን በጥራት እና በፍጥነት ገንብተው በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ ሌት ተቀን እየሰሩ የሚገኙ አመራሮችን፣ ሰራተኞችን፣ ማህበራትን፣ ተቋራጮችን እና ሁሉንም ባለድርሻ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026