🔇Unmute
አሶሳ፤ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ከተረጂነት ለመላቀቅ የተያዘውን ዕቅድ የሚያሳኩ ናቸውሲሉ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ተናገሩ።
የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በተረጂነት ቅነሳና በምግብ ሉዓላዊነት ዙሪያ በተዘጋጀ የ5 ወራት ዕቅድ ላይ ውይይት አድርገዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በውይይቱ ወቅትም እንደተናገሩት፤ ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ከተረጂነት ለመላቀቅ የተያዘውን ዕቅድ የሚያሳኩ ናቸው።
በክልሉ በቅርብ ዓመታት የተጀመረው ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም የመሸፈን ትግበራ አበረታች ውጤት የታየበትና የስራ ባህልን የቀየረ መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይም በቂ ምርትን በመያዝ አደጋን የመቋቋም አቅምን ለማሳደግ እና የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ሙሐመድ አብዱላዚዝ በበኩላቸው፤ የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ አደጋዎችን በራስ አቅም ለመሸፈን በሚደረገው ጥረት በግብርናው ዘርፍ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል።
በዚህም በክልሉ የተለያዩ የግብርና ውጤቶችን በማምረት ለአደጋ ጊዜ ምላሽ ለመስጠት ዝግጅት መደረጉንም አክለዋል።
አሶሳ፤ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ከተረጂነት ለመላቀቅ የተያዘውን ዕቅድ የሚያሳኩ ናቸው ሲሉ የቤ...
Jun 24, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ በአጭር ጊዜ የተገነቡ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራዎች ከተማዋን አዘምነዋታል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸ...
Jun 23, 2026
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026